
ሙሴ ጸሊም ማለት ጥቁሩ ሙሴ ማለት ነው፤ መልኩ ጥቁር ስለሆነ ነው ጥቁሩ ሙሴ ተብሎ የተጠራው፤ በነገራችን ላይ ከዕለታት በአንዱ ቀን በዚሁ በጥቁረቱ የተነሳ አባቶች አንድ ፈተና አቅርበውለት ነበር፣ አባ ኤስድሮስ ይጠሩትና ሙሴ ዛሬ ቀድሰክ ታቆርባለህ ይሉታል እርሱም እሺ አባቴ ብሎ ይወጣል በዚህን ጊዜ አባ እስድሮስ ካህናቶችን ይጠሩና ዛሬ ሙሴ ቅዳሴ ሊቀድስ ወደ መቅደስ ሲገባ ሰድባችሁ አባሩት ብለው ትዕዛዝ ይሰጣሉ እንደተባለው ሙሴ ሊቀድስ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ ወደ መቅደስ ሊገባ ሲል አንተ ጥቁር ብለክ ብለክ ከኛ ጋር መቀደስ አማረክ ወግድ ከዚህ ብለው ያባርሩታል እርሱም ምንም ሳይናገር አንገቱን አቀርቅሮ ትክክል ናቸው ያለ ቦታክ ለምን ገባክ እያለ እራሱን እየወቀሰ ተመለሰ የሚገርመው ቂም ሳይዝባቸው በነጋታው ውኃ ሊቀዳላቸው ሄደ ይህን የተመለከቱ አባ እስድሮስ ጠርተው ሙሴ ያቀረብንልክን ፈተና አልፈካል እግዚአብሔር ካንተ ጋር ይሁን ብለው መርቀውታል። መጽሐፈ መነኮሳት 2ኛው ከአባ ሙሴ ጸሊም ከጻድቁ ተክልዬ በረከት ያሳትፈን።
No comments:
Post a Comment