ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Tuesday 27 November 2012

አባ ገሪማ ዘመደራ

                                                                               †አባ ገሪማ ዘመደራ†


አባ ገሪማ ዘመደራ (“ኦ ወልድዬ ግሩም ገሪማ ገረምከኒ”)

የተሰዓቱ ቅዱሳን ሐዋርያዊ ተልእኮ መቅድም
ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አልአሜዳ በነገሰ በአምስት ዓመት ነው። እንደመጡት እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነው በአክሱም ዐስራ ሁለት ዓመት ኖረዋል።
ተሰዓቱ ቅዱሳን በስም አባ አሌፍ፣ አባ አረጋዊ፣ አባ
 
 ጰንጠሌዎን፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጵሕማ፣ አባ አፍአባ ሊቃኖስ፣ አባ ይምዓታ አባ ጉባ ይባላሉ። እኚ አባቶች ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ዝም ብሎ አልተቀመጡም፤ ለሥራቸው በር ከፋች የሆነውን ቋንቋ፣ የሕዝቡን ባህል ጠንቅቀው ካወቁ በኋላ ላይ በአንድ አከባቢ ከመኖር ይልቅ መንፈስ ቅዱስ በመደባቸው ቀጥታ ማስተማርን መርጠው መንፈሳዊ ዓላማቸውን ለማሳካት የአክሱምን ነገስታት እርዳታና ድጋፍ አልተለያቸውም ነበር። እኚው ተሰዓቱ ቅዱሳን የመጡበት ሀገራት ሮም፣ እስያ፣ አንጾኪያ፣ ቁስጥንጥንያ፣ ቂሳርያ፣ ኪልቂያ ሲሆን በነበሩበት ጊዜያትም፡­-
፩. ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አጽንቶልናል።
፪. መጽሐፍትን ተርጉሞልናል።
፫. ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል።
፬. ብዙ ገዳማትን መስርተዋል።
፭. ሥርዓተ ምንኩስናን አደራጅተዋል።
ስለ እነዚህ ቅዱሳን ይህችን ታህል ካልኩኝ ዛሬ ወርሃዊ ዕለታቸው ከሚታሰበው ከእነዚሁ ቅዱሳን አንዱ ስለሆኑ አባ ገሪማ ዘመደራ ትንሽ ልበላችሁ።
አባ ገሪማ ዘመደራ፡­- ቀዳሚ ስማቸው ይስሐቅ ነው። አባታቸው ሶፎንያስ ንጉስ ሮም ነው። አባ ገሪማ ከልጅነታቸው ጀምሮ በመንፈሳዊ ትምህርት ታንጸው አድገው ቤተ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ ኖረዋል። ኋላም የአባታቸውን ዙፋን ወርሰው ለ፯ ዓመት ገዝተዋል። ከዚህ በኋላ አባ ጰንጠሌዎን “ምድራዊ መንግስት ያልፋል ይጠፋል፤ የማያልፈውን ሰማያዊ መንግስት ትወርስ ዘንድ ፈጥነህ ወደኔ ና።” ብለው ላኩባቸው። ቅዱስ ገብርኤል ከእግዘዚአብሐሔር ታዞ በክንፉ ነጥቆ በአንድ ቀን አክሱም አድርሷቸው ተገኙ። መዓርገ ምንኩስናን ተቀብለው ሥጋቸው አልቆ አጥንታቸው

እንኳን ለኅዳር ጽዮን በሰላም አደረሳችሁ

          እምነ ጽዮን - እናታችን ጽዮን                   

እንኳን ለኅዳር ጽዮን በሰላም አደረሳችሁ
በቅዱሳት መጻሕፍት ጽዮን የሚለው ቃል ተደጋግሞ በነቢያቱ ተነግሯል፡፡ ሆኖም የጽዮን ትርጉም እንደተነገረበት ዐውደ ትንቢት እንደተሰበከበት መዋዕለ ትምህርት ምስጢሩ ይለያያል፡፡
ድንግል ማርያም ምስለ ፍቁር ወልዳ
ታቦተ ጽዮን በፈቃደ እግዚአብሔር በነቢዩ ሙሴ አማካኝነት ለሰው ልጆች ተሰጥታ እስራኤላውያን ሲባረኩባት፣ መሥዋዕታቸውን ሲያቀርቡባት ከእግዚአብሔር ሲታረቁባት ኖረዋል፡፡ከአራት ሺሕ ሦስት መቶ ሃያ ሰባት ዓመተ ዓለም (4327 ዓ.ዓ.) ጀምሮ ለአርባ ዓመታት ያህል እስራኤላውያንን በክህነት ያገለግል የነበረው ካህኑ ዔሊ ዕድሜው ሲገፋ ሁለት ልጆቹን ጠርቶ ምሉዕና ዱግ /ዋናና ምክትል/ አድርጎ ሾማቸው፡፡

Friday 23 November 2012

ሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ

                                           ሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ


ከቅዱሳን
ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ሚና 4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ተጋድሎውን የፈፀመ ግብፃዊ ሰማዕት ሲሆን ህዳር 15 ቀን የሚነበበው ስንክሳር ቅዱስ ሚናስ በሚል ስያሜ ይገልፀዋል። በሶሪያ ቋንቋ ማር የሚለው ቃልቅዱስየሚልትርጉም ሲኖረው ለወንድ የሚሰጥ ቅጥያ ሲሆን ለሴት ደግሞ ማርታ ይሆናል ይሄውም ቅድስት ማለት ነው።
ቅዱስ ሚናስ ከእናቱ ከአውፌምያ እና ከአባቱ ከአውዶስዮስ ልዩ ስሙ ኒቆስ ሻቲ በተባለ መንደር 276 ተወለደ። እናቱ አውፌምያ ልጅ መውለድ ባለመቻሏ ታዝንና ትጨነቅ ነበር። ወደ ቤተ-ክርስቲያን ስትሄድም እናቶች ልጆቻቸውን ሲያቆርቡ ስታይ በማልቀስ ፈጣሪዋን ልጅ እንዲሰጣት ትለምን ነበር። እግዚአብሔርም የልመናዋን ቃል ሰምቶ ወንድ ልጅ ሰጣት።

Thursday 8 November 2012

ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ

                                ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ
ጥቅምት 30 ቀን ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የተወለደበት ቀን ነው፤ በመዲናችን አዲስ አበባ ጨምሮ በስሙ በታነጹለት አብያተ ክርስቲያናት ታቦተ ህጉ ወጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል፤ ሚያዚያ 30 እረፍቱ ነው። ቅዱስ ማርቆስ ቁጥሩ ከ 72ቱ አርድእት ነው፤ የእናቱ ስም ማርያም ይባላል ቁጥሯ ከ 36ቱ ቅዱሳት አንስት ነው፤ በ 50ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደላቸው በዚህች ቅድስት እናት ቤት ሆነው ሲጸልዩ ነው፤ ሐዋ 2፤1 12፤12 ፤ ይህ ሐዋርያ ወንጌሉን የጻፈው ጌታ

Tuesday 6 November 2012

አቡነ መብአ ጽዮን

                 አቡነ መብአ ጽዮን

ጥቅምት 27 ቀን ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ መብአ ጽዮን የእረፍት ቀናቸው ነው፤ ትውልዳቸው ሸዋ ትጉለት ውስጥ ነው:: እመቤታችን ያወጣችላቸው ስም ተክለ ማርያም ነው፤እኚህ ጻድቅ በጣም የሚታወቁበት ተጋድሎ አላቸው፤ ይህም አርብ አርብ ቀን የጌታችንን ሞቱን ለማሰብ ትልቅ ድንጋይ በጀርባቸው አዝለው እልፍ እልፍ እየሰገዱ ማታ ላይ ኮሶ ይጠጡ ነበር፤ ሀሞት መጠጣቱን ለማሰብ፤ ከጽድቃቸው ብዛት የተነሳ መቋሚያቸውን ቢተክሉት ሎሚና ትርንጎ አፈርቷል፤

Sunday 4 November 2012

አባ ሳሙኤልዘዋልድባ

                        አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ



(by Wubishet Tekle )ታሀሳስ 12 በዚህች ቀን ታላቁ ኢትዮጰያዊው ጻድቅ አባ ሳሙኤል አረፈ። የትውልድ ቦታው አክሱም ነው፤ 18 ዓመቱ ከአቡነ መድሐኒነ እግዚ እጅ ምንኩስናን ተቀበለ በዚያው በደብረ ባንኮል 13 ዓመት በተጋድሎ ኖረ፤ከዚያም ወደ ጎንደር ደምቢያ ሄደ 3 ወር ከዘረጋ ሳያጥፍ ከቆመ ሳያርፈ እህል ውኃ ሳይቀምስ በተጋድሎ ኖረ፤ከድካም ብዛት አጥንቱ ተሰብሮ ወደቀ ጌታችን ተገለጸለት አበረታው ያንተ ክፍልህ እዚህ አይደለም ወደ ዋልድባ ሂድ አለው፤ ወደ ዋልድባ ሄደ በዚያም ግርማ ሌሊቱን ድምጸ አራዊቱን ታግሶ ማቅ ለብሶ ድንጋይ ተንተርሶ በተጋድሎ ኖረ። ይህ አባት ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ነበረው ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በቀን 64 64 ጊዜ ይጸልይ ነበር፤ውዳሴዋን እየደገመ መንገድ ሲሄድ ከምድር ክንድ ከስንዝር ከፍ ይላል፤