ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Wednesday 25 December 2013

አባ መቃርስ


  1. ታላቁ መቃርስ ከመልካምና ቅዱሳን ቤተሰብ ሻብሺር መኑፍ በተባለ አከባቢ ተወለደ። አባቱ አብራግ እናቱ ደግሞ ሳራ ይባላሉ። ወንድ ልጅ አልነበራቸውም። አብራግ በሕልሙ የእግዚአሔር መልአክ መጥቶ ወንድ ልጅ ትወልዳላችሁ ስሙም በምድር ሁሉ የታወቀ እንደሚሆንና ብዙ ደቀ መዛሙርን እንደሚያፈራ ገለጸለት።

    ሕጻኑ ሲወለድ ገና መቃርስ አሉት ...ትጉሙም የተባረከ ማለት ነው።

    ሰይጣን በአንድ ወቅት ለአባ መቃርስ ጠላቶችህ በጣም በዙ ሲለው አባ መቃርስ “ሰው የሰው ጠላት የለውም” አለውና ሰይጣንን አሳፈረው! ዲያቢሎስም ታዲያ የሰው ጠላት ማን ነው? ብሎ አባ መቃርስን ጠየቀው። አባ መቃርስም የሰው ጠላትማ የእለተ አርቡን ሰው አዳምን የፈተነ ፣ ኢዮብን ፣ ዳዊትን ፣ የበቁ አባቶችን በሙሉ የፈተነ አንድ ፍጥረት ነበር፤ ጠላት እሱ ነው! “አንተ ይህን ፍጥረት አታውቀውም እንዴ?” አለው። ዲያቢሎስም ኧረ በጭራሽ ሰምቼ አላውቅም አንዳችም የማውቀው ነገር የለኝም፤ ይገርማል! እንዴት ያለ ጨካኝ ነው አለ ራሱን እየነቀነቀ! አባ መቃርስም አዎ እንዳልከው ጨካኝ ነው፤ ይህን ፍጥረት አለማወቅህ ግን ገርሞኛል። ይገርምሃል እሱ ጨካኝ ብቻ ሳይሆን የፈጠረውን በገዳመ ቆሮንጦስ የፈተነ ደፋርም ጭምር ነው። ጨካኝና ደፋር ቢሆንም በጌታችን ድል ተነስቷልና እኛም ይህችን ጾም ሰሞኑን እየጾምን እኮ ነው አለው። ይህን ግዜ “ዲያቢሎስ ድል ተነስቷል” የሚለውን ቃል ሲሰማ ሽንፈቱ ትዝ አለውና ተቁነጠነጠ።እንዳይታወቅበት ግን “አይ ደፋሩ ጉድ ጉድ! እያለ ማስመሰሉን ቀጠለ። አባ መርቃስም እንዴ አንተ ይህን ካላወቅህ አትጾምም ማለት ነው እንዴ? አለው ፈገግ እያለ። ዲያቢሎስም ጾ… ጾ ….. ም…. ጾም ትንሽ ስለሚያመኝ…. እያለ ሲቀባጥር አባ መርቃስ አሁንም ፈገግ እያለ አይ አንተ የሰው ጠላት የምትሆነው እስከ መቼ ነው? መታመሜን አውቀህ እንዳልጾም ይህን ሁሉ ቀባጠርክ። ገና ስትመጣ ማን እንደሆንክ አውቅ ነበር! ገና እኔን ለመፈተን ስታስብ አውቅ ነበር! አይ ዲያቢሎስ የሰው ጠላት አንተ ብቻ ነህ! በል አሁን የጾም ግዜ ነውና ዞር በል ብሎ ገሰፀው። ዲያቢሎስም ከእርሱ ራቀ። ይህን የአባ መቃርስን ታሪክ ሳነብ አንድ ነገር ትዝ አለኝ፤ “ዲያቢሎስ እንደ ሚያገሳ አንበሳ በዙሪያችሁ ይዞራል በእምነት ሆናችሁ ተቃወሙት ከእናንተም ይሸሻል” የምትለዋ የሐዋርያው መልዕክት ፩ኛ ጴጥሮስ [፭:፰] ይህን በደንብ እንረዳ ሰው የሰው ጠላት የለውም፤ ጠላት ማን ነው? ጠላት ዲያቢሎስ ነው።

Friday 6 December 2013

ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ

  1. ♥በስመ ሥላሴ♥
    “ሳጥናኤል ይማር አለም ይዳን”
    ==> ኢትዮጵያዊት ጻድቅ የእምነት ሴት አርበኛ ጻድቅ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ <==
    ጌታም ይህን ሁሉ መከራ እንደ መስዋዕት ቆጥሮላት አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ በተስፋዋ ያመነውን ቃል ኪዳኗ የተማጸነውን እስከ 10 ትውልድ ድረስ እንዲምርላት ተስፋዋን ነግሯታል።
    ==> “የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩ...ኸታቸው ናቸውና …. ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው……የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል…ጻድቃንንም የሚጠሉ ይጸጸታሉ። <== ” መዝ.፴፫፥፲፯¬-፳፩ (33፥17¬-21
    ==> ሀገሯ ቡለጋ ቅድስጌ ልዩ ስሙ ጥጥ ምድር አከባቢ ነው። አባቷ ቅዱስ ደረሳኒ እናቷ ቅድስት እሌኒ ይባላሉ። ቤተሰቦች በክብር በስርዓት ቅድሳት መጽሐፍትን ብሉይ ከሐዲሳት እያስተማሩ ባደገችና ለአካለ መጠን (ለአቅመ ሔዋን) ስትደርስ የመኳንንት የመሳፍንት ልጅ ናትና ለንጉስ ባለሟል ለሆኑ ትውልድ ነገዱ ፃሰርጓ ወገን ሲሆን የኢሱስ ሞዓ ልጅ ሠምራ ጊዮርጊስ ለሚባል ደግ ካህን በሕግ በ14 ዓመቷ ዳሯት። ፲፪ ልጆችም ወልዳለች።
    ==> ከመከራዋ ብዛት ከገድሏ ጽናት ሰውነቷ ተበሳስቶ የዓሣ መመላለሻ እስኪሆን ድረስ ከባህሩ ገብታ ወደ ግራና ቀኝ ሳትል ፲፪ ዓመት ጸለየች። በመጨረሻም ጌታ ምን አደርግልሽ ትሽያለሽ?