ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Monday 10 February 2014

‹‹ጾመ ነነዌ እና የኮብላዊው ነቢይ የዮናስ ተግባር›› በፖፕ ሺኖዳ ሶስተኛ እንደተጻ

                                                                                                      ከሳምሶን ኃ/ሚካኤል

ነገ የሚገባው የነነዌ ጾም መቼም ለኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ከታላቁ ከጌታ ጾም በፊት  በእየአመቱ የሚጾም  ጾም  ነውና በደንብ ይታወቃል ይልቁን  አባቶቻችን እናቶቻችን ‹‹ የነይነይ ጾም›› አስከማለት ደርሰው  ስም አውጥተውላታል፡፡ ስያሜው ከጾመ ነነዌ ወደ ነይነይ  የተቀየረውበንባብ ተፋልሶ ይሁን  ወይም ቶሎ ቶሎ ነይ ለማለት ተፈልጎ …. በእርግጥ አላውቅም፡፡ ወደ ዋናው አሳቤ ስገባ..የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሶስተኛ መጽሀፍ የሆነውን ስለ ነቢዩ ዮናስ የተጻፈውን ‹‹CONTEMPLATIONS ON THE BOOK OF JONAH THE PROPHET ›› የተባለውን መጽሀፍ ሳነብ ወዳጆቼስ ትንሽ ባካፍል ብዬ እንዲህ በውርስ ትርጉም አቀረብኩት፡፡

መጽሀፍ ቅዱሱ ታሪኩን እንዲህ ብሎ ይጀምራል…..‹‹የእግዚአብሔርም ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ እንዲህ ሲል መጣ።ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ።ዮናስ ግን ከእግዚአብሔር ፊት ወደ ተርሴስ ይኰበልል ዘንድ ተነሣ ወደ ኢዮጴም ወረደ፥ ወደ ተርሴስም የምታልፍ መርከብ አገኘ ከእግዚአብሔርም ፊት ኰብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሄድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርስዋ ገባ።››ትንቢተ ዮናስ 11

1.  ‹‹ነቢዩ ዮናስ ራስ ወዳድ ነበር ››