ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Saturday 20 December 2014

መልአኩን ልኮ አዳናቸው

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
                  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታህሣሥ 19 ከከበሩት መላእክት አንዱ የሆነው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክበረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት በመዝሙር በጸሎት በምስጋና በቅዳሴ በዝክር ይከበራል ይታሰባል። የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለሥቱ ደቁቅን ከዕቶነ እሳት(ከነደደ እሳት) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
          ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል ሉቃ 1፥20 
ታላቁ ነብይ ሄኖክ ስለ ነገረ መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መሰክሯል << በባቦች ላይ በገነትም በጸድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው ፡፡>> ሄኖክ 6-7<< በሦስተኛውም  በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ  ቅዱስ  ገብርኤል ነው >>1014 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል