ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Monday 6 July 2015

ምሥጢረ ተክሊል (ክፍል ሰባት , ክፍል ስምንት,ክፍል ዘጠኝ

                                                                           ምሥጢረ ተክሊል ክፍል ሰባት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የወደደን የፍቅር መምህራችን እግዚአብሔር ስለማይነገር ስጦታው ሁሉ ስሙ የተመሰገነ ይሁን፤ የአምላክ እናት ቤዛዊተ ዓለም ድንግል ማርያም በትውልዱ ሁሉ አንደበት ምስጋና ይድረሳት፤ ለስሙ ለተለዩ ቅዱሳን፤ ለስሙ ለሞት ተላልፈው ለተሰጡ ሰማእታት፤ መናፍቃንን ድል ለነሱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፤ ስለ ስሙ ለተሰደዱ ጻድቃን ምስጋና ይሁን፡፡ አሜን፡፡
እርሱ እየረዳን፤እርሱ ድካማችንን እያገዘን፤እርሱ ጎዶሏችንን እየሞላ፤እርሱ ጥያቄዎቻችንን እመለሰ፤እርሱ በጉዟችን ሁሉ ከፊት እየቀደመ ከኋላም እየተከተለ፤ከጎንም እየደገፈን፤ኃይላችን እያደሰ፤በየምዕራፉ እያሳረፈን ከሰባተኛው ክፍል አድርሶናል፡፡ በእውነት ይህም በእርሱ ነውና ክብር ብቻውን አምላክ ለሆነው ለእርሱ ለእግዚአብሔር ይሁን፡፡ አሜን፡፡
ወዳጆቼ እንደ ውቂያኖስ የጠለቀ እንደ ባሕር የሰፋውን የእናት ቤተክርስቲያናችንን ምስጢራት በማንኪያ ታህል እንድንቀምስ የረዳን እግዚአብሔር በክፍል አንድ የምሥጢረ ተክሊል ምንነት፤ በክፍል ሁለት የጋብቻ ዓላማ፤ በክፍል ሦስት ቅድመ ጋብቻን፤በክፍል አራት የቅድመ ጋብቻን የመጨረሻ ክፍል፤በክፍል አምስት ድንግልናና ተክሊል ፤ በክፍል ስድስት የሥርዓተ ተክሊል መስፈርቶች ምንድን ናቸው? በሚሉ ንዑሳን ርዕሶች እርሱ

Thursday 21 May 2015

ምሥጢረ ተክሊል ክፍል አራት ,ክፍል አምስት , ክፍል ስድት



 
                                         ክፍል አራት (4)  ሳሚ ዘቂርቆስ





እግዚአብሔር አባታችን የሚረባንን የሚጠቅመንን እያስተማረን በመንገዳችን ሁሉ እየመራን ረዥሙን ጉዞ አንድ ብለን ጀምረን ይኸው አራተኛው ምዕራፍ ላይ ደረስን አሁንም በቃሉ ምግብነት የተራበችዋን ነፍሳችንን እንዲመግብልን የተቀደሰ ፍቃዱ ይሁን፤ እንደምናስታውሰው በክፍል አንድ የምሥጢረ ተክሊል ምንነትን፤ በክፍል ሁለት የጋብቻ ዓላማን? እንዲሁም በክፍል ሦስት ቅድመ ጋብቻን ጀምረን እንዳይበዛ በማሰብ ይቀጥላል ብለን ማቆማችንን ከወዲሁ ላስታወሳችሁ እወዳለሁ፡፡
ዛሬም እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በክፍል አራት ትምህርታችን የጀመርነውን የቅድመ ጋብቻን ትምህርት እናጠቃልልና ድንግልና እና ተክሊል በሚል ርዕስ ደግሞ በክፍል አምስት እርሱ እንደፈቀደ እንማማራለን፤ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡አሜን
ወዳጆቼ የቀድሞዎቹ ነገስታቶች ክርስትናቸውን አጥብቀው ይይዙ የነበሩ በመሆኑ ይተዳደሩበት የነበረውን መጽሐፍ ፍትሐ ነገስት ማለታቸውን መቅድሙ ይገልፃል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለሀገራችንም ሆነ ለዓለም ሕዝብ የሕግ ምንጭ ሆኖ አሁን ደረስ የሚያገለግል ታላቅ መጽሐፍ ነው፡፡ ከአረበኛ ወደ ግእዝ ቀጥሎም በእንግሊዝኛ እንዲሁም በ1962 ዓ.ም በግእዝ እና በአማረኛ የታተመው መጽሐፍ አገልግሎቱን የዋለው ከ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን(ዓፄ ዘርአያዕቆብ 1444-1468) ጀምሮ ሲሆን የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት እስከ ረቀቀበት(1948 ዓ.ም) ድረስ በዚህ የሕግ መጽሐፍ ኢትዮጵያ ትተዳደርበት እንደነበረ የታሪክ ሕያው ምስክርነትን መጥቀስ ይቻላል፡፡
ወዳጆቼ ቅድመ ጋብቻ ላይ (በምንተጫጭበት ወቅት) ብዙ ጊዜ የማናስተውላቸው እና ከገባንበት በኋላ የምንነቀባቸው ስህተቶች አሉ፡፡

ምሥጢረ ተክሊል ክፍል አንድ, ክፍል ሁለት , ክፍል ሦስት

                                         ክፍል አንድ (1) ሳሚ ዘቂርቆስ

በዚህ ክፍል አንድ ትምህርታችን ምሥጢረ ተክሊል ምንድን ነው? የሚለውን ከብዙ በጥቂቱ እንመለከታለን፡፡
1. ምሥጢረ ተክሊል ምንድን ነው?
ቤተክርስቲያን የክርስቲያን ቤት ናት ፤ጥበብ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤በሰባቱ ምሶሶዎቿ ቤቷን አንጻለች፡፡ እነዚህ ምሶሶዎች ደግሞ የምድር ሥርዓት እስከ ሚጠናቀቅበት ድረስ የማይናዱ፤የማይፈርሱ፤የማይለወጡ፤የማይሻሩ እና አላፊ ያልሆኑ ዘላለማዊ እና ሰማያዊ ጸጋዎችን የሚያሰጡ በሚታይ ነገር ፤ የማይታይን ሀብት ለሁላችን እንድንካፈል የሚያደርጉ ቤተክርስቲያንን በምሶሶነት የሚደግፉ ምሥጢራት ቤተክርስቲያን ናቸው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዲህ ሲል እግዚአብሔር ስላዘጋጀልን ምሥጢራት ይገልጣል፡-" ጥበብ ቤትዋን ሠራች፤ሰባቱንም ምሶሶችዋን አቆመች፡፡ ፍሪዳዋን አረደች፤የወይን ጠጅዋን ደባለቀች፡፡" ምሳ9፡1
ወዳጆቼ ሁላችን እንደምናውቀው በምሶሶ የተመሰሉት ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን፡- 1. ምሥጢረ ጥምቀት 2. ምሥጢረ ቁርባን 3. ምሥጢረ ሜሮን 4. ምሥጢረ ንስሐ 5. ምሥጢረ ክህነት 6. ምሥጢረ ተክሊል 7. ምሥጢረ ቀንዲል ናቸው፡፡

Saturday 20 December 2014

መልአኩን ልኮ አዳናቸው

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
                  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታህሣሥ 19 ከከበሩት መላእክት አንዱ የሆነው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክበረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት በመዝሙር በጸሎት በምስጋና በቅዳሴ በዝክር ይከበራል ይታሰባል። የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለሥቱ ደቁቅን ከዕቶነ እሳት(ከነደደ እሳት) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
          ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል ሉቃ 1፥20 
ታላቁ ነብይ ሄኖክ ስለ ነገረ መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መሰክሯል << በባቦች ላይ በገነትም በጸድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው ፡፡>> ሄኖክ 6-7<< በሦስተኛውም  በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ  ቅዱስ  ገብርኤል ነው >>1014 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል

Saturday 6 September 2014

ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል

በታናሹ ወር በ 3ኛው ቀን በዓሉን አድርጉለት ይኸውም ጳጉሜን ነው ።
ጳጉሜን 3 የመላአክት አለቃ የከበረ መልአክ የሩፋኤል መታሰቢያ ነው ።
ይኸውም ትጉሃን ቅዱሳን ሰማያውያን ከሚሆኑ ከመላአክት አለቆች ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥሎ 3ተኛ ነው ። ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል እግዚአብሔር በ23ቱ ነገደ መላእክት ላይ ሾሞታል፡፡
በዚያች በድህነትና በደስታ ቀን ለሕዝበ ክርስቲያን ከዕፀ ህይወት ይሰጣቸዉ ዘንድ እግዚአብሔር ያዘዘዉ ቅዱስ ሩፋኤልን ነዉ ።
...
ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠብቃቸው እግዚአብሔር እንዳዘዘዉ የሚከፍታቸዉ የሚዘረጋቸዉ ይህ ታላቅ መልአክ ነዉ፡፡
በዚህ ዕለት ተዝካሩ መደረጉ ስለ 2 ነገር ነው የመጀመሪያው በዓለ ሢመቱ ስለሆነ ነው ።
ዳግመኛም የእስክንድርያው ሊቀጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ መሬት ውስጥ 3 ድስት ሙሉ ወርቅ አግኝቶ በአንዱ በድስት ሙሉ ወርቅ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አሰርቷል ። ከእነዱም አንዲቱ ከእስክንድርያ ውጭ በአለች ደሴት ላይ በቅዱስ ሩፋኤል ስም ቤተክርስትያን አሰርቶ ስራዋን ጨርሶ እንደዛሬይቱ በአለች ቀን ቀደሳት ።
ምእመናት ከቤተክርስትያን ውስጥ እየፀለዩ ሳሉ እንሆ ቤተክርስቲያኒቱ ተንቀጠቀጠች ተናወጠች ታወከች ።