ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Sunday 28 April 2013

+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++


+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++

 ፩። ዮሃንስ ፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)

፪። ዳንኤል ፡፡ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው

፫። ኤልሳእ ፡፡ እግዚአብሔር ደህንነት

፬። አሞን ፡፡ የወገኔ ልጅ

፭። እስራኤል ፡፡ የእግዚአብሔር ህዝቦች

፮። ማሪያም ፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ

፯። ሀና ፡፡ ፀጋ

፰። ሩሀማ ፡፡ ምህረት የሚገባት

፱። እያሱ ፡፡ እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት

፲። ጌርሳም፡፡ ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ

፩፩። እዮሳፍጥ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዷል

፩፪። እዮአም ፡፡ አዳኝ

+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++


+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++

 ፩። ዮሃንስ ፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)

፪። ዳንኤል ፡፡ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው

፫። ኤልሳእ ፡፡ እግዚአብሔር ደህንነት

፬። አሞን ፡፡ የወገኔ ልጅ

፭። እስራኤል ፡፡ የእግዚአብሔር ህዝቦች

፮። ማሪያም ፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ

፯። ሀና ፡፡ ፀጋ

፰። ሩሀማ ፡፡ ምህረት የሚገባት

፱። እያሱ ፡፡ እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት

፲። ጌርሳም፡፡ ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ

፩፩። እዮሳፍጥ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዷል

፩፪። እዮአም ፡፡ አዳኝ

Sunday 14 April 2013

ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

Photo: ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6 

መፅሀፍ ቅዱስን የማንበብብ ጥቅም

1. ነፍሳችንን ያድናል ያእ.1:21, 1ጢሞ.4:16, ሮሜ. 1:16, 2ቲሞ.3:15
2. መንፈሳዊ ህይወትን ያሳድጋል (በእምነት በፍቅር በፀጋና ኢውቀት ወ ዘ ተ..) 1ጴጥ.2:2-3, 2ኛ ጴጥ.3:18 ቆላ, 1:9-12, ፊል.1:9-11, 1ኛተሰ.1:2-3, 2ኛ ተሰ.1:3, ፊል4:7
3. ህይወታችንን ያንፃል ይቀድሳል መዝ.(119):9, ዮሀ.15:3, ኤፌ.5:26 ኢሳ.52:11
4. እውነተና የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ወይም ተከታይ ያደርጋል ዮሀ.8:31, ሉቃ.6:40 ማቴ.28:19.20
5. እግዚአብሄርን እንዳንበድል ወይም ሀጢአትን እንዳንሰራ ይገስፀናል መዝ(119):11, 1ቆሮ.10:11 2ጢሞ.3.16:-17, ምሳ.3:11-12, መዝ(141):5
6. ከመለኮት ባህሪ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድንሆን ያደርጋል 2ጴጥ.1:2-4
7. በነፃነት እንድንኖር ወይም ከሀቲአት ባርነት ነፃ እንድንወጣ ያደርጋል ዮሀ.8:31-32, ያእ.1:25, ገላ 5:1
8. እምነት እንዲኖረን ያደርጋል ሮሜ.10:17, እብ.4:2
9. ጥበብንና ማስተዋልን ማግኘት እንድንችል ያደርጋል መዝ.(119):130 መዝ(19):7, መዝ(119):98.100, መሳ.2:1-6 ምሳ.1:2-7, 20-22
10. የሚያጠነክረንና የሚያፀናን ቃል ስለ ሆነ ኢዩ.17:9, መዝ(119):28, ሀዋ.20:32
11. ክፉውን ሁሉ ለማሸነፍ ብርታትን የሚሰጠን ቃል ስለ ሆነ. 1ዮሀ.2:14, ኤፌ.6:13-17
12. የእግዚአብሄርን ሰው ፍፁምና ለበጎ ስራ ሁሉ የተዘጋጀ እንዲሆን ያደርጋል. 2ጢሞ.3:16-17 1ጴጥ.3:15
13. የእግዚአብሄር ቃል ዲያቢሎስን ማሸነፍ ያስችላል.ማቴ.4:1-11, ኤፌ.6:10-18
14. በእግዚአብሄር ፊት የማያሳፍር ሰራተና ሆኖ ለመገኘት በቃሉ መታጠቅ ወይም ቃሉን በትጋት ማጥናት ስለሚያስፈልግ . 2ጢሞ.2:15, መዝ(105):19
15. በመከራችን ጊዜ መፅናናትን ተስፋን ስለሚሰጠን መዝ(119):50, መዝ(55):22, ሮሜ.15:4
16. አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሄር ሰላም የሚገኘው በቃሉ በመኖር ብቻ ስለሆነ መዝ(119):165, ኢሳ.48:17,-19, ኢሳ.54:13, ዮሀ.14:2
17. ለእግራችን መብራት ለመንገዳችንም ብርሀን የሚሆን ቃል ወይም መለኮታዊ ምሪትን የምናገኝበት ቃል ስለሆነ መዝ(119):130, ምሳ.6:23
18. ፈታኝ ሁኔታ ሲያጋጥመን ምላሽ ለመስጠት መዝ.(119)43, ሉቃ. 12:11-12, 1ጴጥ.3:15, ዮሀ.14:26
19. ቃሉ በክፉዎች መናፍስት ላይ ትልቅ ስልጣን ስላለው ማቴ.8:16-17, 8:8, 4:23-25, 15:29-31
20. በህይወታችን ማእበል (ነፋስና ጎርፍ) ሲነሳ እንዳንናወጥ ያደርጋል:: ማቴ.7:24-27, ሉቃ.6:46-49, 1ቆሮ.16:13, 15:58, ኤፌ.4:14-16
21. በቃሉ እውቀት መሞላት የሀሰት ትምህርቶችን ለመከላከልም ሆነ ለማፍረስ ወሳኝ ስለሆነ. ኤር.1:9-10, 23:16-18, ቁጥ.25-32, ዘዳ.13:1-5, ሀዋ.20:29-32, ማቴ.7:14-15, ሮሜ.16-17 -18, 2ጴጥ.2:1-3, 1ዮሀ.4:1-6, 2ዮሀ.7:11
22. ለፀሎታችን መልስ ለማግኘት ያስችለናል. 1ዮሀ.3:
ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ...ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6

የድንግሊቱ ስም››


‹‹የድንግሊቱ ስም››

በዚህ አጠር ያለ ጽሑፍ ውስጥ የእመቤታችንን ስም አጠራሯን ብቻ የሚመለከቱ በአጠቃላይ ሦስት መሠረታዊ ነጥቦችን እንዳስሳለን፡፡

እመቤታችን በብሉይ ኪዳን አበው ሁሉ ዘንድ በብዙ ትንቢቶችና በብዙ ኅብረ አምሳል ትነገር ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ግልጥ ባለ መልኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰችው ቅዱስ ሉቃስ ስለ ብሥራተ መልአክ በተረከበት አንቀጽ ነበር፡፡ መተዋወቅ... ከስም የሚጀምር በመሆኑ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ‹‹የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ›› ሲል የእመቤታችንን ስመ ተጸውዖ በመግለጥ ለዓለም ሁሉ ያስተዋውቃታል፡፡ (ሉቃ1.27)

1ኛ. ስሟ የተለየ ስለመሆኑ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብሉይና በአዲስ ኪዳን ማርያም በሚለው ስም የተጠሩ ከስምንት የማያንሡ ሴቶች አሉ፡፡ የሙሴ እኅት ማርያም፣ ባለሽቱዋ ማርያም፣ መግደላዊት ማርያም፣ የቀለዮጳ ሚስት ማርያም፣ …እያሉ የሁሉንም መጠቀስ ይቻላል፡፡ ነገር ግን አንዳቸውም ከድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክነት በኋላ የተሰየሙ አይደሉም፡፡ ማርያም በሚለው ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ ሴቶች ሁሉ በእርሷ ዘመንና ከእርሷ በፊት የተሰየሙ ናቸው፡፡ ነገር ግን የእቤታችን ክብርና ማዕርግ /ደረጃ/ ይፋ ከሆነ በኋላ ማለትም የአምላክ እናትነቷ ከተገለጠ በኋላ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የተጠራች አንዲትም ሴት የለችም፡፡