ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች
1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ...ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6