ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Tuesday 11 June 2013

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

መልስ-ጸሎት በክርስትና ሕይወት እጅግ አስፈላጊ መሆኑ ጥያቄ የለዉም፡፡በዚህ ጽሑፍ የምንጸልይባቸውን ጊዜያት፣የምንጸልየውን የጸሎ ት ዓይነት፣ ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

1. የጸሎት ጊዜያት

... ልበ አምላክ ነቢየ ልዑል ቅዱስ ዳዊት”ስብዓ ለእለትየ እሴብሐከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ ፣ስለ ጽድቅህ ፍርድ በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለው”/መዝ 118-164/ብሎ እንደተናገረ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሰባት ጊዜ በየእለቱ እንዲጸልይ ቤተ ክርስቲያን ታስተምረናለች፡፡ሰባቱ የጸሎት ጊዜያትም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1.1 ጸሎተ ነግህ

ቅዱስ ዳዊት “አምላኬ አምላኬ በማለዳ ወደ አንተ እገሰግሳለሁ” መዝ 62÷11 እንዳለ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ ሲተካ፣ከመኝታችን ስንነሳ ምንጸልየው የጸሎት ዓይነት ጸሎተ ነግህ ይባላል፡፡በዚህ ጊዜ የሚከተሉትን ምስጢራት እያሰብን መጸለይ ይገባናል፡፡
==>ሌሊቱን አሳልፎ ቀኑን ስለተካልን እያመሰገንን ወጥተን እስክንገባ በሰላም ጠብቆ ውሎአችንን የተባረከ እንዲያደርግልን እንጸልያለን።
==>የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረበትም ሰዓት በመሆኑ ያንን እያሰብን እንጸልያለን፡፡
==>የሰውን ልጅ በመዓልትና በሌሊት የሚጠብቁ መላእክት ለተልዕኮ ሲፋጠኑ የሚገናኙበት ሰዓት ነው፡፡የሌሊቱ መልአክ ሲሄድ የቀኑ መልአክ ሲቀርብና ሲተካ የሚገናኙበት በመሆኑ በዚህም ሰዓት እንጸልያለን፡፡
==>ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች በደል በጲላጦስ አደባባይ የቆመበት ሰዓት በመሆኑ
እንጸልያለን።

1.2 ጸሎተ ሠለስት (3 ሰዓት)

የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መስቀሉ ስር


††† የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መስቀሉ ስር ቆማ ሆድን መሚያቃጥል አንጀትን በቢቆራርጥ በጽኑ ሃዘን ታለቅስ ታነባ ነበር፤

††† በድንግልና ስለፅነሰችው በድንግልና ስለወለደቸዉ ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጽንዋ ሰለተሸከመችዉ ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† በድን...ግልና ስላጠባችው ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ከሃገር ሃገር ተጉዛ በግብጽ በራሃ ስለተንከራተተችበት ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ራሄል ለልጆችዋ የምታለቅስ ከሆነ ድንግል ማርያም ስለተወደደዉ ልጅዋ ለምን አታለቅስ፤
††† ራሄል ከአንድ ቦታ ወደአንድ ቦታ ይዛቸዉ ላልተሰደደቻቸዉ ልጅዎችዋ የምታለቅስ ከሆነ ድንግል ማርያም በስደትና በሰቃይ ወደ በረሃ ይዛው ለተሰደደችዉ ልጅዋ ልምን አታለቅስ፤
††† መቃብራቸዉን ላላየችው ልጅዎችዋ ራሄል የምታለቅስ ከሆነች ድንግል ማርያም የታተመ የልጅዋን መቃብር እያየች ለምን አታለቅስ፤
††† የ12 ነገድ አባት ሽማግሌዉ ያእቆብ ስለልጁ ስለዮሴፍ ያለቀሰዉ ለቅሶ ዛሬ አዲስ ሆኖ ተገኜ፤
††† ያእቆብ ልጁ ዮሴፍን ወንድሞቹ ሲያስሩት አላየም ድንግል ማርያም ግን ልጇ በመስቀል ላይ ተቼንክሮ አይታዋለች፤
††† ያእቆብ ወንድሞቹ ዮሴፍን ከጉድጋድ ሲጥሉት አላየም ፤ ድንግል ማርያም ግን በአይሁድ አደባባይ ልጇ ተሰቅሎ አይታዋለች፤
††† ያእቆብ ወንድሞቹ ልብሱን ገፈው ሲሼጡት አላየም ፤ ድንግል ማርያም ግን ይሁዳ ልጇ በ30 ብር ሲሸጡት አይታለች፤
††† ያእቆብ በልጁ ደም ሳይሆን የበግ ደም አይቶ ነዉ ያለቀሰዉ ፤ መለኮት የተዋሃደዉ የክርስቶስ ደም ግን ድንግል በምታለቅስበት አለት ላይ ፈሰሰ ፤ ስለዚህ አለቀሰች ፤

ስለተወደደ ልጇ ድንግል ለምን አታለቅስ†††


††† ሰባቱ የመላእክት አለቆች መጥተዉ አረጋግዋት ፤ አጽናንዋት እርሷ ግን በመስቀል ላይ የተሰቀለዉ ልጇ እያየች ለቅሶ መተዉን መጽናናትም አልተዎችም፤
††† አባትዋ ዳዊት እሳት በሆነ ፈረስ መጥቶ አጽናናት እርሷ ግን ለቅሶ መተዉን አልቻለችም ፤ እስከ ሶስት ቀን ድረስም እህል ውሃ አላለችም፤