ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Sunday 3 November 2013

ምሥጢረ ንስሐ


 ምሥጢረ ንስሐ
ንስሐ ፦ ነስሐ ተፀፀተ ካለው የተገኘ ሲሆን ፤ ንስሐ ማለት በሠሩት ኃጢአት መፀፀት ፣ ማዘን ፣ ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ መወሰን ፤ ማለት ነው ። ንስሐ ከዘለዓለማዊ ፍርድ የሚያድን ፤ ዘማዊውን እንደ ድንግል ፤ ሌባውን መጽዋች የሚያደርግ በፊት ከተሠራው ኃጢአት ንጹህ አድርጎ ፤ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ የሚያደርግ  ምሥጢር ነው ።
ንስሐ ፦ ከንስሐ በፊት ፣ በንስሐ ጊዜ ፣ ከንስሐ በኋላ፤ ተብሎ  በሶስት ይከፈላል
ከንስሐ በፊት
1 መፀፀት ፤ አንድ ክርስቲያን በድፍረትም ይሁን በስህተት “የሠራው በደል” መጻሕፍት በማንበብ ፣ ከመምህራን ተምሮ ፣ የስብከት ካሴት አዳምጦ ፤ ህሊናው ወቅሶት ፣ ወይም በሌላ በአንድ ምክንያት ስህተት መሆኑን ከተረዳ በኋላ ተፀፅቶ ከእግዚ አብሔር ለመታረቅ (በደሉን ለማስተስረይ) የሚያደርገው ጉዞ ንስሐ ይባላል ። በሠራው በደል ሳይፀፀት ፤ ለጊዜው ህሊናውን ስለረበሸው ብቻ ንስሐ የሚገባ ሰው ፤ ንስሐውን ከጨረሰ በኋላ ወደ ቀደመ ሕይወቱ ሊመለስ ይችላል ። ምክንያቱም ፡ ንስሐ የገ ባው ፡ በሰራው በደል ከልቡ ተፀፅቶ አስቦበት ሳይሆን ፤ በስሜት ተነሳስቶ ነውና ፤ ስሜቱ ሲጠፋ ሥጋዊ ፍላጎቱም ይነሳሳበትና ውሳኔውንም ሊለውጠው ይችላል ።