ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Sunday 30 September 2012

እንኳን ለ ግሸን ማርያም ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !

 

እንኳን ለንጽሕተ ንጹሓን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ - የግማደ መስቀሉ መገኛ ♥†♥†♥† ታላቅ ክብረ በዓል አደረሳችሁ!!!!

✙ ✙ ✙ ግማደ መስቀሉ ከጎሎጎታ እስከ ግሸን ደብረ ከርቤ ✙ ✙ ✙

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት በስላጣኑ ከተነሳ በሗላ መስቀሉ ቀን ከማታ ያበራ ነበረ። አይሁድ ቀንተው ቀበሩትና የቆሻሻ መጣያ እንዲሆን አወጁ። ከ300 ዘመን በሗላ የንጉስ ቆስጠንጢኖስ እናት ንግስት እሌኒ ከቁስጥንጥኒያ መታ የክርስቶስን መስቀል አስቆፍራ ለማውጣት በጸሎት 7 ቀን ከቆየች በሗላ መላኩ ዑራኤል ተገልጾ ደመራ አስደምረሽ በእሳት አያይዘሽ በዛ ላይ ብዙ እጣን አድርጊ የእጣኑ ጢስ ወደ ላይ ወቶ መስቀሉ ያለበትን ቦታ ያሳይሻል አላት። እንዳላትም አድርጋ መስከረም 10 ቀን 370 ዓ.ም ሃይላችን የሆነው መስቀሉ ተገኘ።

Saturday 29 September 2012

ቅዱስ ገብርኤል

ቅዱስ ገብርኤል





በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ በክርስቲያኖች ዘንድ ይወደዳል፡፡ ምክንያቱም ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካልና፡፡
ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል ጌታና አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱሳን ሰማእታት ገድላቸውን እንዲፈጽሙ እሳቱንና ስለቱን ተሳቀው ወደ ኋላ እንዳይመለሱ ይረዳቸዋል፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን የቅዱሳን መላእክትን ወርኃዊና ዓመታዊ በዓላቸውን በፀሎትና በምሥጋና ታከበራለች፤ በተለይ ታህሣሥ 19 ቀን የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለሥቱ ደቁቅን ከዕቶነ እሳት ( ከነደደ እሳት ) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡

Wednesday 26 September 2012

አቡነ እሰትነፋሰ ክርሰቶሰ

እሰትነፋሰ ክርሰቶሰ  አባቱ መላከ ወለተ ማርያም የባላሉ።በመጀመሪያም መላኩ መጥቶ ለናቱ መልካም ልጅ እንደምትወልድ ነገራት። አገሩ ዳውንት ደላነታ አውራጃ ሲሆን በ24 አመቱ መነኮሰ ገዳሙን አቡነ አትናቲዎሰ አድሰወታል። ይህ ገዳም እጅግ ባለ ታሪክ ነው የተመረጠ በመሆኑ በመላእክት የተመሰከረለት ከአደገ በኃላም በሶሰት አመቱ ወደ ሐይቅ እሰቲፋኖሰ ገዳም ገበቶ ያገለገለ የተማረ ነው።ወደ ሐይቅም ሲደረሱ የሚያሻግረው ሲያጣ መልአኩ ደንገል ያቀረበለትና በዚያተሻግሮ ወደ ገዳሙ የገባ ሲጸልይም አቡነ አረጋዊና አጼ ገበረ መስቀል ቅዱሰ ያሬድ  ተገልጸው ያነጋገሩት አባት ነው።
በዚህ በራሱ ገዳም በአሰጂ ከበረሃ ላይ ውሀ አፍልቆ ተማሪዎቹን ያጠጣ ጻድቅ ነው።ያም ፀበል ዛሬ ህሙም ፈዋሸ ሆኖ የሚገኝ ነው። ጻዲቁ በአርማኒያ በዝቋላ በኢየሩሳሌም  በሽዋ በግብጽ ተመላልሷል።
ይህ ጻድቅ በታማኝነቱ ተመርጦ ከንጉሱ ተልኮ የንጉሱን ልጅ የጎንደሩን ጻድቁ ዮሐንሰን እያሰተማረ ያሳደገ ነው።በዚህ ገዳም በቅሎዎች ናቸው የ 9 ሰዓት መንገድ ሄደው ወርደው ከበሸሎ ወንዝ ውሃ መንገደኛው ቀድቶ ሲጭናቸው ሳያጋድሉ የ 9  ሰዓት ምላሽ መንገድ ተጉዘው ከገዳሙ ይገባሉ። ይህ ለጻድቁ የተሰጠ ቃል ኪዳን ነው። የጻድቁን ገዳም የቆረቆረውና የተከለው አቡነ ቤዛ ወልድ የተባለው ጻድቅ ነው። የጻድቁም እረፍት በሚያዝያ ፱ ቀን ከአቡነ ማርቆሰ ግበጻዊ ቅሰና ቁምሰን ተቀበለ። በየካቲት 9 የመነኮሰበት ቀን ነው።የመነኮሰውም በሐይቅ ገዳም ነው በዚህ ገዳም 11 አመት በሹሁመት አገልግሏል። በሰሙም ሁለት ቤተ ክርሰቲያን ተተክለዋል።ወር በገባ በ 9 የአቡነ እሰትነፋሰ ክርሰቶሰ መታሰቢያ ነው የጻድቁ አባታችን የአቡነ እሰትነፋሰ ክርሰቶሰ በረከት በሁላች ላይ ይደር አሜን !!!!!!