ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Saturday 6 September 2014

ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል

በታናሹ ወር በ 3ኛው ቀን በዓሉን አድርጉለት ይኸውም ጳጉሜን ነው ።
ጳጉሜን 3 የመላአክት አለቃ የከበረ መልአክ የሩፋኤል መታሰቢያ ነው ።
ይኸውም ትጉሃን ቅዱሳን ሰማያውያን ከሚሆኑ ከመላአክት አለቆች ከቅዱስ ሚካኤልና ከቅዱስ ገብርኤል ቀጥሎ 3ተኛ ነው ። ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል እግዚአብሔር በ23ቱ ነገደ መላእክት ላይ ሾሞታል፡፡
በዚያች በድህነትና በደስታ ቀን ለሕዝበ ክርስቲያን ከዕፀ ህይወት ይሰጣቸዉ ዘንድ እግዚአብሔር ያዘዘዉ ቅዱስ ሩፋኤልን ነዉ ።
...
ሰማያዉያን መዛግብት በእጁ የሚጠብቃቸው እግዚአብሔር እንዳዘዘዉ የሚከፍታቸዉ የሚዘረጋቸዉ ይህ ታላቅ መልአክ ነዉ፡፡
በዚህ ዕለት ተዝካሩ መደረጉ ስለ 2 ነገር ነው የመጀመሪያው በዓለ ሢመቱ ስለሆነ ነው ።
ዳግመኛም የእስክንድርያው ሊቀጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ መሬት ውስጥ 3 ድስት ሙሉ ወርቅ አግኝቶ በአንዱ በድስት ሙሉ ወርቅ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አሰርቷል ። ከእነዱም አንዲቱ ከእስክንድርያ ውጭ በአለች ደሴት ላይ በቅዱስ ሩፋኤል ስም ቤተክርስትያን አሰርቶ ስራዋን ጨርሶ እንደዛሬይቱ በአለች ቀን ቀደሳት ።
ምእመናት ከቤተክርስትያን ውስጥ እየፀለዩ ሳሉ እንሆ ቤተክርስቲያኒቱ ተንቀጠቀጠች ተናወጠች ታወከች ።

Monday 1 September 2014

አባ ሙሴ ጸሊም

    ሰኔ 24 በዚህች ቀን ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አባ ሙሴ ጸሊም አረፈ፡፡ አስቀድሞ ሽፍታ፣ ወንበዴ፣ ዘማዊ ፣ጣኦት አምላኪ ነበር፤ በኃላ እንደ አብርሃም አምላኬ ማን ነው? ብሎ ተመራመረ፤ ወደ አስቄጥስ ገዳም ብትሄድ አምላክህ ማን እንደሆነ ይነግሩሃል የሚል ራዕይ አየ፣ ተመለከተ፤ ተነስቶም ሄደ አባ ኤስድሮስን አገኛቸው፤አጽናንተው አረጋግተው ወደ አባ መቃርስ ወሰዱት አባ መቃርስም ንስሃውን ተቀብለው ቀኖና ሰጡት ኋላም አመነኮሱት የሽፍቶች አለቃ የነበረው የመነኮሳት አለቃ እስከመሆን ደረሰ፤ ሰይፉን ወርውሮ ከፍቅር ጋር ተወዳጀ፤ሌሊት እየተነሳ ለሁሉም መነኮሳት ውኃ ይቀዳላቸው ነበር፤ ለሁሉም ይታዘዛቸው ነበር ትንሹም ትልቁም ሙሴ ይህን አድርግሊኝ ይሉታል አርሱም ሁሉንም እሺ ይላል፤ ራሱን ዝቅ አደረገ ትሁትም ሆነ፤ በጸሎቱ ዝናብ ያዘንም ነበር፤ እድሜው መጨረሻ አካባቢ ቡራኬ ሊቀበል ከመነኮሳት ጋር ሆኖ ወደ አባ መቃርስ ሄደ አርሳቸውም ልጆቼ ከእናንተ መካከል በሰማእትነት የሚሞት አለ ብለው ትንቢት ተናገሩ ሙሴ ጸሊምም አባቴ ሰው እኔ ነኝ ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ የሚል ቃል አለ ይህን ጊዜ በጉጉት ስጠባበቀው ነበር አላቸው፤ እንደተባለውም የበርበር ሰዎች ገዳሙን ሊያጠፉ መጡ መነኮሳቱ ሲሸሹ ሙሴ እዚያው ቀረ ሌሎች ሰባት መነኮሳት ከአባታችን ጋር እንሞታለን ብለው አብረውት ሆኑ የበርበር ሰዎች ደረሱ ሁሉንም በሰይፍ ገደሏቸው፤ ይህም ሰኔ 24 ቀን ነው፤ የአባታችን የሙሴ ጸሊም ስጋው በገዳመ አስቄጥስ በክብር ይገኛል፤ ግብጻውን ቤተ ክርስቲያን ሰርተውለት ታቦት ቀርጸውለት