ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Tuesday, 11 June 2013

የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መስቀሉ ስር


††† የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መስቀሉ ስር ቆማ ሆድን መሚያቃጥል አንጀትን በቢቆራርጥ በጽኑ ሃዘን ታለቅስ ታነባ ነበር፤

††† በድንግልና ስለፅነሰችው በድንግልና ስለወለደቸዉ ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጽንዋ ሰለተሸከመችዉ ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† በድን...ግልና ስላጠባችው ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ከሃገር ሃገር ተጉዛ በግብጽ በራሃ ስለተንከራተተችበት ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ራሄል ለልጆችዋ የምታለቅስ ከሆነ ድንግል ማርያም ስለተወደደዉ ልጅዋ ለምን አታለቅስ፤
††† ራሄል ከአንድ ቦታ ወደአንድ ቦታ ይዛቸዉ ላልተሰደደቻቸዉ ልጅዎችዋ የምታለቅስ ከሆነ ድንግል ማርያም በስደትና በሰቃይ ወደ በረሃ ይዛው ለተሰደደችዉ ልጅዋ ልምን አታለቅስ፤
††† መቃብራቸዉን ላላየችው ልጅዎችዋ ራሄል የምታለቅስ ከሆነች ድንግል ማርያም የታተመ የልጅዋን መቃብር እያየች ለምን አታለቅስ፤
††† የ12 ነገድ አባት ሽማግሌዉ ያእቆብ ስለልጁ ስለዮሴፍ ያለቀሰዉ ለቅሶ ዛሬ አዲስ ሆኖ ተገኜ፤
††† ያእቆብ ልጁ ዮሴፍን ወንድሞቹ ሲያስሩት አላየም ድንግል ማርያም ግን ልጇ በመስቀል ላይ ተቼንክሮ አይታዋለች፤
††† ያእቆብ ወንድሞቹ ዮሴፍን ከጉድጋድ ሲጥሉት አላየም ፤ ድንግል ማርያም ግን በአይሁድ አደባባይ ልጇ ተሰቅሎ አይታዋለች፤
††† ያእቆብ ወንድሞቹ ልብሱን ገፈው ሲሼጡት አላየም ፤ ድንግል ማርያም ግን ይሁዳ ልጇ በ30 ብር ሲሸጡት አይታለች፤
††† ያእቆብ በልጁ ደም ሳይሆን የበግ ደም አይቶ ነዉ ያለቀሰዉ ፤ መለኮት የተዋሃደዉ የክርስቶስ ደም ግን ድንግል በምታለቅስበት አለት ላይ ፈሰሰ ፤ ስለዚህ አለቀሰች ፤

ስለተወደደ ልጇ ድንግል ለምን አታለቅስ†††


††† ሰባቱ የመላእክት አለቆች መጥተዉ አረጋግዋት ፤ አጽናንዋት እርሷ ግን በመስቀል ላይ የተሰቀለዉ ልጇ እያየች ለቅሶ መተዉን መጽናናትም አልተዎችም፤
††† አባትዋ ዳዊት እሳት በሆነ ፈረስ መጥቶ አጽናናት እርሷ ግን ለቅሶ መተዉን አልቻለችም ፤ እስከ ሶስት ቀን ድረስም እህል ውሃ አላለችም፤

Sunday, 28 April 2013

+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++


+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++

 ፩። ዮሃንስ ፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)

፪። ዳንኤል ፡፡ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው

፫። ኤልሳእ ፡፡ እግዚአብሔር ደህንነት

፬። አሞን ፡፡ የወገኔ ልጅ

፭። እስራኤል ፡፡ የእግዚአብሔር ህዝቦች

፮። ማሪያም ፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ

፯። ሀና ፡፡ ፀጋ

፰። ሩሀማ ፡፡ ምህረት የሚገባት

፱። እያሱ ፡፡ እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት

፲። ጌርሳም፡፡ ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ

፩፩። እዮሳፍጥ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዷል

፩፪። እዮአም ፡፡ አዳኝ

+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++


+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++

 ፩። ዮሃንስ ፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)

፪። ዳንኤል ፡፡ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው

፫። ኤልሳእ ፡፡ እግዚአብሔር ደህንነት

፬። አሞን ፡፡ የወገኔ ልጅ

፭። እስራኤል ፡፡ የእግዚአብሔር ህዝቦች

፮። ማሪያም ፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ

፯። ሀና ፡፡ ፀጋ

፰። ሩሀማ ፡፡ ምህረት የሚገባት

፱። እያሱ ፡፡ እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት

፲። ጌርሳም፡፡ ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ

፩፩። እዮሳፍጥ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዷል

፩፪። እዮአም ፡፡ አዳኝ

Sunday, 14 April 2013

ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

Photo: ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6 

መፅሀፍ ቅዱስን የማንበብብ ጥቅም

1. ነፍሳችንን ያድናል ያእ.1:21, 1ጢሞ.4:16, ሮሜ. 1:16, 2ቲሞ.3:15
2. መንፈሳዊ ህይወትን ያሳድጋል (በእምነት በፍቅር በፀጋና ኢውቀት ወ ዘ ተ..) 1ጴጥ.2:2-3, 2ኛ ጴጥ.3:18 ቆላ, 1:9-12, ፊል.1:9-11, 1ኛተሰ.1:2-3, 2ኛ ተሰ.1:3, ፊል4:7
3. ህይወታችንን ያንፃል ይቀድሳል መዝ.(119):9, ዮሀ.15:3, ኤፌ.5:26 ኢሳ.52:11
4. እውነተና የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ወይም ተከታይ ያደርጋል ዮሀ.8:31, ሉቃ.6:40 ማቴ.28:19.20
5. እግዚአብሄርን እንዳንበድል ወይም ሀጢአትን እንዳንሰራ ይገስፀናል መዝ(119):11, 1ቆሮ.10:11 2ጢሞ.3.16:-17, ምሳ.3:11-12, መዝ(141):5
6. ከመለኮት ባህሪ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድንሆን ያደርጋል 2ጴጥ.1:2-4
7. በነፃነት እንድንኖር ወይም ከሀቲአት ባርነት ነፃ እንድንወጣ ያደርጋል ዮሀ.8:31-32, ያእ.1:25, ገላ 5:1
8. እምነት እንዲኖረን ያደርጋል ሮሜ.10:17, እብ.4:2
9. ጥበብንና ማስተዋልን ማግኘት እንድንችል ያደርጋል መዝ.(119):130 መዝ(19):7, መዝ(119):98.100, መሳ.2:1-6 ምሳ.1:2-7, 20-22
10. የሚያጠነክረንና የሚያፀናን ቃል ስለ ሆነ ኢዩ.17:9, መዝ(119):28, ሀዋ.20:32
11. ክፉውን ሁሉ ለማሸነፍ ብርታትን የሚሰጠን ቃል ስለ ሆነ. 1ዮሀ.2:14, ኤፌ.6:13-17
12. የእግዚአብሄርን ሰው ፍፁምና ለበጎ ስራ ሁሉ የተዘጋጀ እንዲሆን ያደርጋል. 2ጢሞ.3:16-17 1ጴጥ.3:15
13. የእግዚአብሄር ቃል ዲያቢሎስን ማሸነፍ ያስችላል.ማቴ.4:1-11, ኤፌ.6:10-18
14. በእግዚአብሄር ፊት የማያሳፍር ሰራተና ሆኖ ለመገኘት በቃሉ መታጠቅ ወይም ቃሉን በትጋት ማጥናት ስለሚያስፈልግ . 2ጢሞ.2:15, መዝ(105):19
15. በመከራችን ጊዜ መፅናናትን ተስፋን ስለሚሰጠን መዝ(119):50, መዝ(55):22, ሮሜ.15:4
16. አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሄር ሰላም የሚገኘው በቃሉ በመኖር ብቻ ስለሆነ መዝ(119):165, ኢሳ.48:17,-19, ኢሳ.54:13, ዮሀ.14:2
17. ለእግራችን መብራት ለመንገዳችንም ብርሀን የሚሆን ቃል ወይም መለኮታዊ ምሪትን የምናገኝበት ቃል ስለሆነ መዝ(119):130, ምሳ.6:23
18. ፈታኝ ሁኔታ ሲያጋጥመን ምላሽ ለመስጠት መዝ.(119)43, ሉቃ. 12:11-12, 1ጴጥ.3:15, ዮሀ.14:26
19. ቃሉ በክፉዎች መናፍስት ላይ ትልቅ ስልጣን ስላለው ማቴ.8:16-17, 8:8, 4:23-25, 15:29-31
20. በህይወታችን ማእበል (ነፋስና ጎርፍ) ሲነሳ እንዳንናወጥ ያደርጋል:: ማቴ.7:24-27, ሉቃ.6:46-49, 1ቆሮ.16:13, 15:58, ኤፌ.4:14-16
21. በቃሉ እውቀት መሞላት የሀሰት ትምህርቶችን ለመከላከልም ሆነ ለማፍረስ ወሳኝ ስለሆነ. ኤር.1:9-10, 23:16-18, ቁጥ.25-32, ዘዳ.13:1-5, ሀዋ.20:29-32, ማቴ.7:14-15, ሮሜ.16-17 -18, 2ጴጥ.2:1-3, 1ዮሀ.4:1-6, 2ዮሀ.7:11
22. ለፀሎታችን መልስ ለማግኘት ያስችለናል. 1ዮሀ.3:
ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ...ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6

የድንግሊቱ ስም››


‹‹የድንግሊቱ ስም››

በዚህ አጠር ያለ ጽሑፍ ውስጥ የእመቤታችንን ስም አጠራሯን ብቻ የሚመለከቱ በአጠቃላይ ሦስት መሠረታዊ ነጥቦችን እንዳስሳለን፡፡

እመቤታችን በብሉይ ኪዳን አበው ሁሉ ዘንድ በብዙ ትንቢቶችና በብዙ ኅብረ አምሳል ትነገር ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ግልጥ ባለ መልኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰችው ቅዱስ ሉቃስ ስለ ብሥራተ መልአክ በተረከበት አንቀጽ ነበር፡፡ መተዋወቅ... ከስም የሚጀምር በመሆኑ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ‹‹የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ›› ሲል የእመቤታችንን ስመ ተጸውዖ በመግለጥ ለዓለም ሁሉ ያስተዋውቃታል፡፡ (ሉቃ1.27)

1ኛ. ስሟ የተለየ ስለመሆኑ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብሉይና በአዲስ ኪዳን ማርያም በሚለው ስም የተጠሩ ከስምንት የማያንሡ ሴቶች አሉ፡፡ የሙሴ እኅት ማርያም፣ ባለሽቱዋ ማርያም፣ መግደላዊት ማርያም፣ የቀለዮጳ ሚስት ማርያም፣ …እያሉ የሁሉንም መጠቀስ ይቻላል፡፡ ነገር ግን አንዳቸውም ከድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክነት በኋላ የተሰየሙ አይደሉም፡፡ ማርያም በሚለው ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ ሴቶች ሁሉ በእርሷ ዘመንና ከእርሷ በፊት የተሰየሙ ናቸው፡፡ ነገር ግን የእቤታችን ክብርና ማዕርግ /ደረጃ/ ይፋ ከሆነ በኋላ ማለትም የአምላክ እናትነቷ ከተገለጠ በኋላ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የተጠራች አንዲትም ሴት የለችም፡፡

Saturday, 16 March 2013

አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ ማቴ.4፥2

አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ ማቴ.4፥2 አትም ኢሜይል

የካቲት 29/2004 ዓ.ም.
በመ/ር ምሥጢረሥላሴ ማናየ
ይህ ከላይ ያነሣነው ርዕስ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት መጾሙን ያስተምረናል፡፡
በዚህ ኀይለ ቃል ሁለት ታላላቅ ቁም ነገሮችን ቃላትን እንመለከታለን
  1. አርባ መአልትና አርባ ሌሊት
  2. ጾም የሚሉት ናቸው፡፡

በቅድሚያ አርባ መአልትና አርባ ሌሊት የሚለውን ከእነ ምስጢሩ እንመለከተዋለን፡፡ ቀጥለን ደግሞ ጌታችንስ ለምን አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ? የሚለውን እንመለከታለን እግዚአብሔር አይነልቡናችንን ይክፈትልን፡፡

እግዚአብሔር አምላካችን የፈጠረውን የሰው ልጆችን አባት አዳምን፣ በልጅነት አክብሮ ገነት ያስገባው በፈጠረው በአርባ ቀኑ ነው፡፡ “ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ዘገብሮ ለአዳም” አዳምን የፈጠረ እግዚአብሔር ቅዱስ ነው እያሉ እያመሰገኑ መላእክት ወደገነት አስገብተውታል /ቀሌ.4፥/

“ወላምድኅረ ተፈጸመ ለአዳም ፵ መዋዕል በምድር ኀበ ተፈጥረ አባዕናሁ ውስተ ገነተ ኤዶም ኩፋ.9፥12 ለአዳም አርባ ቀን ከተፈጸመለት በኋላ ወደገነት አስገባነው፡፡ ሔዋንንም በሁለት አርባ ማለትም በሰማኒያ ቀኑዋ ወደገነት አስገቧት ኩፋ.4፥12

በተጨማሪም አዳም ትእዛዘ እግዚአብሔር ካፈረሰ በኋላ ዲያብሎስ በአቋራጭ መጥቶ አስወጣው እንጂ ሱባኤ የገባው ለአርባ ቀናት ነበር፡፡ ይህን አርባ ቀን የሰው ልጆች ከስህተት በኋላ በቀንም ሆነ በዓመት ለጾም፣ ለሱባኤ፣ ከዚያ አልፎ ለመቅጫነት አግልሏል፡፡

Monday, 11 March 2013

ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር ዘፍ.35፥1

ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር ዘፍ.35፥1 አትም ኢሜይል

የካቲት 27 ቀን 2005 ዓ.ም.
ዲ/ን ሰለሞን መኩሪያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
ይህንን የተናገረ አምላካችን እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ የተነገረው እስራኤል ለተባለ ያዕቆብ ነው፡፡
በቅዱስ መጽሐፍ ታሪኩ ተጽፎ እንደምናገኘው ከወንድሙ ከዔሳው ሸሽቶ የአባቱን የይስሐቅን በረከት ተቀብሎ ወደ አጎቱ ወደ ላባ ሲሄድ ሎዛ ከምትባለው ምድር ሲደርስ ጊዜው መሸ፡፡ እርሱም ደክሞት ስለነበር ድንጋይ ተንተርሶ ተኝቶ ሳለ ሌሊት በራእይ እግዚአብሔር ተገለጠለት ራእዩም የወርቅ መሰላል ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ በመሰላሉ መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም በዙፋኑ ተቀምጦ ነበር፡፡ ያዕቆብንም “እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ፤ አትፍራ፣ ይህችን አንተ የተኛህባትን ምድር ለአንተም ለዘርህም እሰጣለሁ ዘርህም እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናል፡፡ በአንተ በዘርህ አሕዛብ ይባረካሉ፡፡ እነሆም እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፡፡ የነገርኩህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህም” አለው፡፡ ያዕቆብም ከእንቅልፍ ተነሥቶ በእውነት እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ አለ፤ እኔ አላወቅሁም ነበር፡፡ ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራል? ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህችም የሰማይ ደጅ ናት፡፡ ያዕቆብም ማልዶ ተነሣ ተንተርሷት የነበረችውንም ድንጋይ ወስዶ ሐውልት አድርጎ አቆማት፤ በላይዋም ዘይት አፈሰሰባት፡፡ ያዕቆብም ያን ሥፍራ ቤቴል ብሎ ጠራው አስቀድሞ ግን የዚያ ከተማ ስም ሎዛ ነበር፡፡ ያዕቆብም ስዕለትን ተሳለ፡፡ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ቢሆን በምሄድበት መንገድ ቢጠብቀኝ፣ የምበላውን እንጀራ የምለብሰውን ልብስ ቢሰጠኝ ወደ አባቴ አገር በሰላም ቢመልሰኝ እግዚአብሔር አምላኬ ይሆንልኛል፡፡ ለሐውልት ያቆምኳት ይህች ድንጋይ የእግዚአብሔር ቤት ትሆንልኛለች፤ ከሰጠኸኝ ሁሉ ለአንተ ከአስር እጅ አንዱን እሰጥሃለሁ አለ፡፡ እግዚአብሔርም ስእለቱን ሰምቶ ሁሉንም ፈጸመለት ወደ አጎቱ ወደ ላባ ደርሶ ሚስት አግብቶ ብዙ ልጆችን ወልዶ እንዲሁም ብዙ ባሮችን እና ሀብት ንብረት አፍርቶ ወደ አባቱ ሀገር ሲመለስ እግዚአብሔር አምላክ ተገለጠለትና “ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር” ብሎ አዘዘው ዘፍ.28፥10-20፣ ዘፍ.35፥1፡፡
ለመሆኑ ይህች ቤቴል ማን ናት? እግዚአብሔር አምላክ ለጊዜው ያዕቆብና ቤተሰቡ እንዲኖሩባት ለፍጻሜው ሁላችንም እንድንኖርባት የታዘዝንባት ቤቴል ምስጢራዊ ትርጉሟ ምን ይመስላል? አባቶቻችን እንዲህ ይተረጉሙታል፡፡