ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Wednesday, 31 July 2013

ትምህርተ ጋብቻ ክፍል ፦ ፩

    ከ መልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው ብሎግ የተወሰደ
http://www.betedejene.org/2010/12/blog-post.html
፩፦ « መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር ነው፤» ዕብ ፲፫፥፬
          ጋብቻን ባርኮና ቀድሶ ለሰው ልጅ የሰጠው እግዚአብሔር ነው። በመሆኑም ጋብቻ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው። ስለዚህ በዓይን ምኞት ተጋርደው፥ በሥጋ ፍላጐት ተነድተው ፥ በስሜት ፈረስ ጋልበው ፥ የሚገቡበት ሳይሆን ፦ በጸሎት እና በምልጃ ፈቃደ እግዚአብሔርን ጠይቀው የሚፈጽሙት ታላቅ ምሥጢር ነው።
          ጋብቻ የሰው ሁሉ ሕልም ነው። የማይመኘው፥የማይፈልገው የለም። የሰው  ሁሉ ጸሎት፥ የሰው ሁሉ ስእለት ነው። ለመሆኑ፦ ህልሙ የተፈታለት ፥ ጸሎቱ የደረሰለት ፥ ስዕለቱ የሰመረለት ስንቱ ይሆን? ያላገባው ይናፍቃል ፥ ያገባው ደግሞ ያማርራል። ከጋብቻ በፊት « መልአክ » የተባለ የትዳር ጓደኛ ከጋብቻ በኋላ «ሰይጣን» ይባላል። «እኔ የመረጥኩትን ካላገባሁ እሰቀላለሁ፤» እንዳልተባለ «ካልተፋታሁ መርዝ እጠጣለሁ፤» ለማለት ችግር የለም። ከጋብቻ በፊት ምክር ላለመስማት አሳብ ላለመቀበል፦ «ስለ እኔ ማንም አያገባውም፤» ተብሎ በር እንዳልተዘጋ ሁሉ ከጋብቻ በኋላ ግን ጣልቃ የማያስገቡት ሰው  የለም ፤ «ምን በወጣህ ፥ ምን በወጣሽ፤» የሚለውን ፈጥኖ ለመቀበል በሩ ለሁሉም ክፍት ነው።
፪፦ ጋብቻ እንዴት ተጀመረ?

          ጋብቻ በአዳምና በሔዋን እንደተጀመረ የጎላ፥ የተረዳ ፥ የታወቀ ነገር ነው። «ተባዕተ ወአንስተ ገብሮሙ፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፤ » እንዲል፦ አዳም ሲፈጠር ሔዋን በውስጡ ነበረች። ዘፍ ፩፥፳፰። ይህም በባህርዩ ነበረች ማለት ነው። አንድ አካል፥ አንድ ሥጋ ከሚያሰኛቸው ምሥጢር አንዱና ዋነኛውም ይኸው ነው።
          ጋብቻ የተጀመረው በአዳም ጥያቄ ነው፤ ጥያቄዎም የኅሊና ማለትም ውሳጣዊ ነበር። ምክንያቱም፦ ከላይ እንደተ መለከትነው፦ የትዳር ጓደኛው በውስጡ ስለነበረች ነው። « እግዚአብሔር አምላክም፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት፥አለ፤»ይላል። እግዚአብሔር እንዲህ ማለቱ፦ በአዳም ኅሊና ውስጥ ይህ ጥያቄ እንደሚነሣ ስለሚያውቅ ነው። መናገሩም ለአዳም ኅሊና እንጂ ፥ ሔዋን ለአዳም እንደምትፈጠርለት አስቀድሞ በእግዚአብ ሔር ዘንድ የተወሰነ ነው።

Tuesday, 11 June 2013

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ?

መልስ-ጸሎት በክርስትና ሕይወት እጅግ አስፈላጊ መሆኑ ጥያቄ የለዉም፡፡በዚህ ጽሑፍ የምንጸልይባቸውን ጊዜያት፣የምንጸልየውን የጸሎ ት ዓይነት፣ ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

1. የጸሎት ጊዜያት

... ልበ አምላክ ነቢየ ልዑል ቅዱስ ዳዊት”ስብዓ ለእለትየ እሴብሐከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ ፣ስለ ጽድቅህ ፍርድ በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለው”/መዝ 118-164/ብሎ እንደተናገረ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሰባት ጊዜ በየእለቱ እንዲጸልይ ቤተ ክርስቲያን ታስተምረናለች፡፡ሰባቱ የጸሎት ጊዜያትም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1.1 ጸሎተ ነግህ

ቅዱስ ዳዊት “አምላኬ አምላኬ በማለዳ ወደ አንተ እገሰግሳለሁ” መዝ 62÷11 እንዳለ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ ሲተካ፣ከመኝታችን ስንነሳ ምንጸልየው የጸሎት ዓይነት ጸሎተ ነግህ ይባላል፡፡በዚህ ጊዜ የሚከተሉትን ምስጢራት እያሰብን መጸለይ ይገባናል፡፡
==>ሌሊቱን አሳልፎ ቀኑን ስለተካልን እያመሰገንን ወጥተን እስክንገባ በሰላም ጠብቆ ውሎአችንን የተባረከ እንዲያደርግልን እንጸልያለን።
==>የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረበትም ሰዓት በመሆኑ ያንን እያሰብን እንጸልያለን፡፡
==>የሰውን ልጅ በመዓልትና በሌሊት የሚጠብቁ መላእክት ለተልዕኮ ሲፋጠኑ የሚገናኙበት ሰዓት ነው፡፡የሌሊቱ መልአክ ሲሄድ የቀኑ መልአክ ሲቀርብና ሲተካ የሚገናኙበት በመሆኑ በዚህም ሰዓት እንጸልያለን፡፡
==>ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች በደል በጲላጦስ አደባባይ የቆመበት ሰዓት በመሆኑ
እንጸልያለን።

1.2 ጸሎተ ሠለስት (3 ሰዓት)

የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መስቀሉ ስር


††† የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መስቀሉ ስር ቆማ ሆድን መሚያቃጥል አንጀትን በቢቆራርጥ በጽኑ ሃዘን ታለቅስ ታነባ ነበር፤

††† በድንግልና ስለፅነሰችው በድንግልና ስለወለደቸዉ ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጽንዋ ሰለተሸከመችዉ ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† በድን...ግልና ስላጠባችው ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ከሃገር ሃገር ተጉዛ በግብጽ በራሃ ስለተንከራተተችበት ልጅዋ ድንግል ማርያም ለምን አታለቅስ፤
††† ራሄል ለልጆችዋ የምታለቅስ ከሆነ ድንግል ማርያም ስለተወደደዉ ልጅዋ ለምን አታለቅስ፤
††† ራሄል ከአንድ ቦታ ወደአንድ ቦታ ይዛቸዉ ላልተሰደደቻቸዉ ልጅዎችዋ የምታለቅስ ከሆነ ድንግል ማርያም በስደትና በሰቃይ ወደ በረሃ ይዛው ለተሰደደችዉ ልጅዋ ልምን አታለቅስ፤
††† መቃብራቸዉን ላላየችው ልጅዎችዋ ራሄል የምታለቅስ ከሆነች ድንግል ማርያም የታተመ የልጅዋን መቃብር እያየች ለምን አታለቅስ፤
††† የ12 ነገድ አባት ሽማግሌዉ ያእቆብ ስለልጁ ስለዮሴፍ ያለቀሰዉ ለቅሶ ዛሬ አዲስ ሆኖ ተገኜ፤
††† ያእቆብ ልጁ ዮሴፍን ወንድሞቹ ሲያስሩት አላየም ድንግል ማርያም ግን ልጇ በመስቀል ላይ ተቼንክሮ አይታዋለች፤
††† ያእቆብ ወንድሞቹ ዮሴፍን ከጉድጋድ ሲጥሉት አላየም ፤ ድንግል ማርያም ግን በአይሁድ አደባባይ ልጇ ተሰቅሎ አይታዋለች፤
††† ያእቆብ ወንድሞቹ ልብሱን ገፈው ሲሼጡት አላየም ፤ ድንግል ማርያም ግን ይሁዳ ልጇ በ30 ብር ሲሸጡት አይታለች፤
††† ያእቆብ በልጁ ደም ሳይሆን የበግ ደም አይቶ ነዉ ያለቀሰዉ ፤ መለኮት የተዋሃደዉ የክርስቶስ ደም ግን ድንግል በምታለቅስበት አለት ላይ ፈሰሰ ፤ ስለዚህ አለቀሰች ፤

ስለተወደደ ልጇ ድንግል ለምን አታለቅስ†††


††† ሰባቱ የመላእክት አለቆች መጥተዉ አረጋግዋት ፤ አጽናንዋት እርሷ ግን በመስቀል ላይ የተሰቀለዉ ልጇ እያየች ለቅሶ መተዉን መጽናናትም አልተዎችም፤
††† አባትዋ ዳዊት እሳት በሆነ ፈረስ መጥቶ አጽናናት እርሷ ግን ለቅሶ መተዉን አልቻለችም ፤ እስከ ሶስት ቀን ድረስም እህል ውሃ አላለችም፤

Sunday, 28 April 2013

+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++


+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++

 ፩። ዮሃንስ ፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)

፪። ዳንኤል ፡፡ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው

፫። ኤልሳእ ፡፡ እግዚአብሔር ደህንነት

፬። አሞን ፡፡ የወገኔ ልጅ

፭። እስራኤል ፡፡ የእግዚአብሔር ህዝቦች

፮። ማሪያም ፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ

፯። ሀና ፡፡ ፀጋ

፰። ሩሀማ ፡፡ ምህረት የሚገባት

፱። እያሱ ፡፡ እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት

፲። ጌርሳም፡፡ ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ

፩፩። እዮሳፍጥ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዷል

፩፪። እዮአም ፡፡ አዳኝ

+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++


+++በብሉይ ኪዳን ውስጥ ካሉ ስሞች ከነትርጓሜያቸው በጥቂቱ++

 ፩። ዮሃንስ ፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ (ሀሴት፣ ፍስሀ)

፪። ዳንኤል ፡፡ እግዚአብሔር ፈራጅ ነው

፫። ኤልሳእ ፡፡ እግዚአብሔር ደህንነት

፬። አሞን ፡፡ የወገኔ ልጅ

፭። እስራኤል ፡፡ የእግዚአብሔር ህዝቦች

፮። ማሪያም ፡፡ የእግዚአብሔር ስጦታ

፯። ሀና ፡፡ ፀጋ

፰። ሩሀማ ፡፡ ምህረት የሚገባት

፱። እያሱ ፡፡ እግዚአብሔር አዳኝ ነው፣ መድሃኒት

፲። ጌርሳም፡፡ ከሌላ ምድር ስደተኛ ነኝ

፩፩። እዮሳፍጥ፡፡ እግዚአብሔር ፈርዷል

፩፪። እዮአም ፡፡ አዳኝ

Sunday, 14 April 2013

ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

Photo: ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6 

መፅሀፍ ቅዱስን የማንበብብ ጥቅም

1. ነፍሳችንን ያድናል ያእ.1:21, 1ጢሞ.4:16, ሮሜ. 1:16, 2ቲሞ.3:15
2. መንፈሳዊ ህይወትን ያሳድጋል (በእምነት በፍቅር በፀጋና ኢውቀት ወ ዘ ተ..) 1ጴጥ.2:2-3, 2ኛ ጴጥ.3:18 ቆላ, 1:9-12, ፊል.1:9-11, 1ኛተሰ.1:2-3, 2ኛ ተሰ.1:3, ፊል4:7
3. ህይወታችንን ያንፃል ይቀድሳል መዝ.(119):9, ዮሀ.15:3, ኤፌ.5:26 ኢሳ.52:11
4. እውነተና የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ወይም ተከታይ ያደርጋል ዮሀ.8:31, ሉቃ.6:40 ማቴ.28:19.20
5. እግዚአብሄርን እንዳንበድል ወይም ሀጢአትን እንዳንሰራ ይገስፀናል መዝ(119):11, 1ቆሮ.10:11 2ጢሞ.3.16:-17, ምሳ.3:11-12, መዝ(141):5
6. ከመለኮት ባህሪ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድንሆን ያደርጋል 2ጴጥ.1:2-4
7. በነፃነት እንድንኖር ወይም ከሀቲአት ባርነት ነፃ እንድንወጣ ያደርጋል ዮሀ.8:31-32, ያእ.1:25, ገላ 5:1
8. እምነት እንዲኖረን ያደርጋል ሮሜ.10:17, እብ.4:2
9. ጥበብንና ማስተዋልን ማግኘት እንድንችል ያደርጋል መዝ.(119):130 መዝ(19):7, መዝ(119):98.100, መሳ.2:1-6 ምሳ.1:2-7, 20-22
10. የሚያጠነክረንና የሚያፀናን ቃል ስለ ሆነ ኢዩ.17:9, መዝ(119):28, ሀዋ.20:32
11. ክፉውን ሁሉ ለማሸነፍ ብርታትን የሚሰጠን ቃል ስለ ሆነ. 1ዮሀ.2:14, ኤፌ.6:13-17
12. የእግዚአብሄርን ሰው ፍፁምና ለበጎ ስራ ሁሉ የተዘጋጀ እንዲሆን ያደርጋል. 2ጢሞ.3:16-17 1ጴጥ.3:15
13. የእግዚአብሄር ቃል ዲያቢሎስን ማሸነፍ ያስችላል.ማቴ.4:1-11, ኤፌ.6:10-18
14. በእግዚአብሄር ፊት የማያሳፍር ሰራተና ሆኖ ለመገኘት በቃሉ መታጠቅ ወይም ቃሉን በትጋት ማጥናት ስለሚያስፈልግ . 2ጢሞ.2:15, መዝ(105):19
15. በመከራችን ጊዜ መፅናናትን ተስፋን ስለሚሰጠን መዝ(119):50, መዝ(55):22, ሮሜ.15:4
16. አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሄር ሰላም የሚገኘው በቃሉ በመኖር ብቻ ስለሆነ መዝ(119):165, ኢሳ.48:17,-19, ኢሳ.54:13, ዮሀ.14:2
17. ለእግራችን መብራት ለመንገዳችንም ብርሀን የሚሆን ቃል ወይም መለኮታዊ ምሪትን የምናገኝበት ቃል ስለሆነ መዝ(119):130, ምሳ.6:23
18. ፈታኝ ሁኔታ ሲያጋጥመን ምላሽ ለመስጠት መዝ.(119)43, ሉቃ. 12:11-12, 1ጴጥ.3:15, ዮሀ.14:26
19. ቃሉ በክፉዎች መናፍስት ላይ ትልቅ ስልጣን ስላለው ማቴ.8:16-17, 8:8, 4:23-25, 15:29-31
20. በህይወታችን ማእበል (ነፋስና ጎርፍ) ሲነሳ እንዳንናወጥ ያደርጋል:: ማቴ.7:24-27, ሉቃ.6:46-49, 1ቆሮ.16:13, 15:58, ኤፌ.4:14-16
21. በቃሉ እውቀት መሞላት የሀሰት ትምህርቶችን ለመከላከልም ሆነ ለማፍረስ ወሳኝ ስለሆነ. ኤር.1:9-10, 23:16-18, ቁጥ.25-32, ዘዳ.13:1-5, ሀዋ.20:29-32, ማቴ.7:14-15, ሮሜ.16-17 -18, 2ጴጥ.2:1-3, 1ዮሀ.4:1-6, 2ዮሀ.7:11
22. ለፀሎታችን መልስ ለማግኘት ያስችለናል. 1ዮሀ.3:
ለመፅሀፍ ቅዱስ ጥናት የሚያስፈልጉ መንፈሳዊ መርሆዎች

1.መፅሀፍ ቅዱስን ማክበርና በተሰበረ ልብ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኢሳ.66:2. 57:15
2. የመፅሀፍ ቅዱስን ጥቅምና ዋጋ በመረዳት ማጥናት:: 2ጢሞ.3:15-17, መዝ.119:105, 29:3-9
3. በእግዚአብሄር መንፈስ መሪነትና አብሪነት ማጥናት:: 1ቆሮ.2:11 1ዮሀ.2:20-21:27
4. ለመፅሀፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ...ሊኖር ይገባል:: መዝ.119:47-48,97
5. በፀሎት መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል::ሉቃ.24:44, መዝ.119:17,ቆላ.4:3-4,ኤፌ.6:18:-20
6. በመታዘዝ መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.119.166-168 ያእ.1:22
7. በትጋት ዘወትር ሳያቁዋርጡ ማጥናት ያስፈልጋል:: መዝ.1:2, 119:123, ኢያሱ.1:8, ዘዳ.17:18-20
8. በጥማትና በናፍቆት ማጥናት:: መዝ.119:40,131, ማቴ.5:6
9. ንፁህ ልብና ህይወት ያስፈልጋል:: ህዝ.18:30-31, እብ.12:14, ዘፀ.19:10-11
10. በተዘጋጀና ንቁ አእምሮና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ፊሊ4:6-7
11. በሙሉ ልብና መንፈስ ማጥናት ያስፈልጋል:: ኤር.29:13, መዝ.119:69
12. ፀጥተኛና አመቺ ቦታ ማዘጋጀት. ኢሳ.30:15
13. በዝግታና በማስተዋል ማንበብብ.
14. እግዚአብሄር በቃሉ እንደሚናገረን መጠበቅ. ራኢይ.3:7, መዝ.85:8
15. የተወሰነ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል መጥኖ ማንበብ.
16. ያልተረዱት ክፍል ሲገጥም የሌሎችን እገዛ መጠየቅ. ሀዋ.8:30-31
17. የተረዱትን እውነት ባማስታወሻ መያዝ
18. ያነበቡትን ክፍልና መልእክቱን ማሰላሰል. መዝ.119:15-16, 97:99
19. መልእክቱን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ለማደረግ መጣጣር. መዝ.119:133, ያእ.1:22-25
20. መልእክቱን ለለሎች ማካፈል. እዝ.7:10, ሮሜ.10:10, ገላ.6:6

የድንግሊቱ ስም››


‹‹የድንግሊቱ ስም››

በዚህ አጠር ያለ ጽሑፍ ውስጥ የእመቤታችንን ስም አጠራሯን ብቻ የሚመለከቱ በአጠቃላይ ሦስት መሠረታዊ ነጥቦችን እንዳስሳለን፡፡

እመቤታችን በብሉይ ኪዳን አበው ሁሉ ዘንድ በብዙ ትንቢቶችና በብዙ ኅብረ አምሳል ትነገር ነበር፡፡ በአዲስ ኪዳን ግልጥ ባለ መልኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰችው ቅዱስ ሉቃስ ስለ ብሥራተ መልአክ በተረከበት አንቀጽ ነበር፡፡ መተዋወቅ... ከስም የሚጀምር በመሆኑ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ‹‹የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ›› ሲል የእመቤታችንን ስመ ተጸውዖ በመግለጥ ለዓለም ሁሉ ያስተዋውቃታል፡፡ (ሉቃ1.27)

1ኛ. ስሟ የተለየ ስለመሆኑ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብሉይና በአዲስ ኪዳን ማርያም በሚለው ስም የተጠሩ ከስምንት የማያንሡ ሴቶች አሉ፡፡ የሙሴ እኅት ማርያም፣ ባለሽቱዋ ማርያም፣ መግደላዊት ማርያም፣ የቀለዮጳ ሚስት ማርያም፣ …እያሉ የሁሉንም መጠቀስ ይቻላል፡፡ ነገር ግን አንዳቸውም ከድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክነት በኋላ የተሰየሙ አይደሉም፡፡ ማርያም በሚለው ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ ሴቶች ሁሉ በእርሷ ዘመንና ከእርሷ በፊት የተሰየሙ ናቸው፡፡ ነገር ግን የእቤታችን ክብርና ማዕርግ /ደረጃ/ ይፋ ከሆነ በኋላ ማለትም የአምላክ እናትነቷ ከተገለጠ በኋላ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የተጠራች አንዲትም ሴት የለችም፡፡