ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Thursday 27 December 2012

ታኅሣሥ ገብርኤል

                                                       ታኅሣሥ ገብርኤል

ገብርኤል ማለትእግዚእ ወገብር” -የእግአብሔር አገልጋይ ማለት ነው። ፍጥረታት መፈጠር በጀመሩበት በዕለተ እሑድ እግዚአብሔር መላእክትን ከፈጠራቸው በኋላ ተሰወራቸው መላእክትምመኑ ፈጠረነ፡ ማን ፈጠረንሲሉ ዲያብሎስ እኔ ፈጠርኳችሁ ብሎ መላእክት በተረበሹ ጊዜየፈጠረንን አምላካችን እስክናውቅ በያለንበት ጸንተን እንቁምብሎ ያረጋጋቸው መልአክ ነው። በዚህም ምክንያት ጌታበእንተዝ ይደልዎ ከመ ይጹር ዜናሃ ለማርያምእንዲል ሥጋዌውን ለድንግል እንዲያበስር አድሎታል። ከዚህም በኋላ ደጋግ ሰዎችን ለመርዳት የሚወጣ የሚወርድ ሆኗል።ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ በክርስቲያኖች ዘንድ ይወደዳል፡፡ ምክንያቱም ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካልና፡፡
በዚህም ዕለት በታህሳስ 19 እግዚአብሔር አገልጋይ የሆኑትን አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ከእቶነ እሳት አድኗቸዋል። (ትንቢተ ዳንኤል ዕራፍ 3)
ነገሩ እንደዚህ ነው -

Tuesday 25 December 2012

አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና ሥራዎቹ - ክፍል 1

 
ዜና ሕይወቱ ለአባ ጊዮርጊስ
ልደቱ
የወርቃማው ዘመን ወርቃማ ደራሲ፣ መናኝ፣ ጻድቅ፣ ሊቅ፣ የሕዝብ መምህር እና የሥነ ምሕንድስና ባለሙያ የሆነው አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የተወለደው በ03፻፶7 ዓመተ ምሕረት በወሎ ክፍለ ሀገር በዛሬው ቦረና በጥንቱ ወለቃ ወረዳ ሸግላ በተባለ ቦታ ነው፡፡ አባቱ ሕዝበ ጽዮን እናቱ እምነ ጽዮን ይባላሉ፡፡ ስለ አባቱ ሕዝበ ጽዮን ሁለት የተለያዩ ታሪኮች ይተረካሉ፡፡ የሰኔ ድርሳነ ዑራኤል ምንባብ አባቱ በመጀመሪያ የትግራይ በማስከተል የሰግላ /ጋሥጫ/ አገር ገዢ እንደነበር ይወሳል፡፡ ገድሉ ደግሞ /ጠቢብ ወማእምረ መጻሕፍት ወአቡሁኒ መፍቀሬ እግዚአብሔር አምኁልቈ ካህናተ ደብተራ ዘውሳጤ ዓጸደ ቤተ ንጉሥ/ አባቱም የእግዚአብሔር ወዳጅና በቤተ መንግሥት በነበረችው ድንኳን /ሥዕል ቤት/ ከሚያገለግሉ ካህናት ወገን ነበረ ይላል፡፡ እንደ ገድሉ ገጸ ምንባብ ትርጉም ሕዝበ ጽዮን ከንጉሡ ሥዕል ቤት በቅዳሴ ወይም በማሕሌት ከሚያገለግሉ ካህናት አንዱ ነው፡፡ /. . . ወእሙኒ እም ሥዩማነ ወለቃ/ እናቱም ከወለቃ ሹማምንት ወገን ነች ይላታል፡፡ ይኸውም የጥንቱ ወለቃ /የዛሬው ደቡብ ወሎ፣ ቦረና ከላላ/ ከነበሩ መኳንንት ወገን መሆኗን ያመለክታል፡፡ የአባ ጊዮርጊስ ወላጆች ልጅ ሳይወልዱ ለረጅም ዓመታት ቆይተዋል፡፡ የልጅ ፍላጎታቸው እንዲሠምር ለሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተሳሉ፡፡ ስእለታቸውም ሥምሮ በመልአኩ ቀዱስ ዑራኤል አብሣሪነት ወንድ ልጅ ወለዱ፡፡ ልጃቸውን ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን በመማጸን ስለወለዱ ስሙን ጊዮርጊስ ብለው ጠሩት፡፡ ወላጆቹ የታላቁን ሰማዕት ስም ለልጃቸው ያወጡት ወደ ፊት በዓላውያን ነገሥታት ፊት ምስክር፣ አፅራረ አምነትን አሳፋሪ፣ ካህናትንና ምእመናት በየዘመናቱ ከሚነፍሱ የኑፋቄና የክህደት ነፋሳት በወንጌል ብርሃን ነፃ የሚያወጣ ሲሉ ይህን ስም እንዳወጡለት ድርሳነ ዑራኤል እንዲህ ይተርካል፡፡ ‹‹ዘይከውን መምህረ ኵሉ ዓለም ወበጸሎቱ ዘያድኅን አሞተ ሲኦል ፍቁረ ድንግል ማርያም ወላዲቱ ለአማኑኤል፡፡ ወመገሥጾሙ ለነገሥት፡፡ ወፀሮሙ ለዐላውያን ሃይማኖት በሰይፈ ቃሎሙ ለሐዋርያት ዘያጠፍኦሙ እም ብሔረ ኢትዮጵያ፤ ወለካህናተ ጽድቅ ዘይመርሆሙ እምጽልመተ ኑፋቄ መንገለ ብርሃን ቃለ ወንጌሉ ለክርስቶስ በትምህርተ ሕጎሙ ለሐዋርያት›› ይላል፡፡

አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫና ሥራዎቹ - ክፍል 2

ምንኵስናና ተጋድሎ
ዐፄ ዳዊት የአባ ጊዮርጊስን ሊቅነትና መልካም ሥነ ምግባር በሚገባ ስላወቀ በጋብቻ ሊዛመደው ወዶ ስለ ነበር ልጁን እንዲያገባ ዘወትር ይጠይቀው ነበር፡፡ አባ ጊዮርጊስ ግን በድንግልና ጸንቶ ለመኖር እንደ ሚገልግ ከመግለጽ አልተቆጠበም ነበር፡፡ የዐፄ ዳዊት ጥያቄ ስለበዛበት ከአካባቢው በመሸሽ ከአባ በጸሎተ ሚካኤል መቃብር ደረሰ፡፡ አባ በጸሎተ ሚካኤልን ከልጅነቱ ጀምሮ ይወዳቸው ስለነበር እርሳቸው በመሠረቱት ገዳም በመልካም ሥነ ምግባራቸው ከታወቁት የአባ ቴዎድሮስ ዘንድ የምንኵስና ልብስ ለብሶ መነኮሰ፡፡
ከመነኮሰ በኋላ ወደ ሸግላ በመምጣት ‹‹ወእምድኀረዝ ኮነ አቡነ ጊዮርጊስ መምህር ለነገሥት ወለካህናት ዘደብተራ ወለኩሉ ዐበይተ ቤተ መንግሥት፣ ለንቡራነእድ ወለመኳንንት፣ ለመሳፍነት ወለኩሉ ተዐይነ ቤተ መንግሥት ከዚህ በኋላ ለነገሥታትና በቤተ መንግሥቱ ለነበሩ ካህናት እንዲሁም በቤተ መንግሥቱ ታላላቆች ለነበሩ፣ ለንቡራነእድ ለመኳንንት፣ ለመሳፍንትና በቤተ መንግሥቱ ለነበሩ ባለሟሎች ሁሉ መምህር ሆነ፡፡››
አባ ጊዮርጊስ በሸግላ በነበረ ጊዜ በወባ በሽታ ታምሞ ሊሞት ደርሶ እንደ ነበር ገድሉ ይናገራል፡፡ታምሞ በነበረ ጊዜ አንድ ሌሊት ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ ተገልጠውለት ከእኛ ጋር ትኖር ዘንድ ልንወስድህ መጣን አሉት፡፡ እርሱም የድርሰት ሥራዬን ሳልሠራና እግዚአብሔርንም አብዝቼ ሳላመሰግነው አሁን አትውሰዱኝ ሲል ለመነ፡፡ እነርሱም ልመናውን ተቀብለውት ከሕመሙ ፈውሰውት ሔዱ፡፡ ለዚህም ይመስላል ከበሽታው እንደ ተፈወሰ ወዲያው የድርሰት ሥራውን የጀመረው፡፡
የመጀመሪያ መጽሐፉን ጽፎ እንደ ጨረሰ ጠፍቶበት እንደ ነበር ገድሉ ይተርካል፡፡ በቤቱ ውስጥ የነበሩትን መጻሕፍት ሁሉ እያገላበጠ ቢፈልገውም ሊያገኘው አልቻለም፡፡ አንድ ቀን በቤተክርስቲያን ሌሊት በአገልግሎት ላይ እያለ እመቤታችን ተገልጣ

Sunday 23 December 2012

የቅዱስ መስቀሉ መቀበር

ሰገደ ጢስ (ጢስ ሰገደ)
ልዑል እግዚአብሔር ኃይሉንና ድንቅ
ሥራዎቹን ከሚገልጽባቸው ሥነ ፍጥረቶቹ
መካከል አንዱና ዋነኛው ራሱ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል
ነው፡፡ ዕፀ መስቀሉ ጌታችን ክብር ምስጋና
ይድረሰውና በደል ሳይኖርበት ዓለምን ለማዳንና
የሰውን ልጅ ሁሉ ከኃጢአትና ከበደል ነፃ
ለማድረግ ሲል እንደ በደለኛ ከአመፀኞች
ጋራ ተቆጥሮ አይሁድ በግፍ በሰቀሉት ጊዜ
ክቡር አካሉ ያረፈበትና እጅ እግሩ በችንካር
ጎኑ በጦር ተወግቶ ደሙ የፈሰሰበት
በመሆኑ ከዕፅዋት ሁሉ የላቀ ክብርና ሞገስ
ያለው ቅዱስ ነው፡፡
ስለሆነም የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክቡር ደሙ ያከበረው በቅዱስ ሥጋው የቀደሰውና መለኮታዊ ኃይሉና ባሕርያዊ ሕይወቱ ያረፈበት ሰለሆነ ኃይልን ሕይወትን ፈውስን ጽናትን የሚሰጥ ሆኖ በገቢረ ተአምርነቱ እየተገለጸና እየታወቀ በመሄዱ መስቀል የእግዚአብሔር ኃይልና የጥበቡ መገለጫ ነው፡፡ ጌታ ከትንሣኤውና ከዕርገቱ በኋላ ድውዮችን በመፈወስ ሙታንን በማስነሳት አንካሶችንና ዕውሮችን በማዳን ተአምራቱንና ኃይሉን መግለጽ የጀመረውም በቅዱስ መስቀሉ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ የዳኑትና ይህን ድንቅ ተአምር የተመለከቱ ሁሉ ሕይወትና ቤዛ የመሆን ጸጋ የተሰጠው መሆኑን እያመኑ መስቀል ኃይላችን መስቀል ቤዛችን መስቀል የነፍሳችን መድኃኒት ነው እያሉ የጸጋና የአክብሮት ስግደት የሚሰግዱለት ሁነዋል፡፡
የቅዱስ መስቀሉ መቀበር
Meskelአይሁድ ግን ቅዱስ መስቀሉ በፊታቸው ልዩ ልዩ ተአምራትንና ብዙ ምልክቶችን ሲያደርግ እያዩ ማመን ተሳናቸው ቀደም ሲል ጌታ በመካከላቸው በሕይወት /በአካል/ እየተመላለሰ በሽተኞቻቸውን እየፈወሰ ሙታኖችን እያስነሳና ኅብስት አበርክቶ እየመገበና ብዙ ተአምራት እያደረገ ቢያስተምራቸው ቀንተው ተመቅኝተው ገርፈውና ሰቅለው እንደገደሉት ሁሉ ይህንም ቅዱስ መስቀል ወደ ቆሻሻ ቦታ ከመጣላቸውም በላይ መሬት ቆፍረው ቀብረውት ነበር፡፡

Wednesday 12 December 2012

ታኅሣሥ 3 እረፍቱ ለአቡነ ዜና ማርቆስ

ታኅሣሥ 3 እረፍቱ ለአቡነ ዜና ማርቆስ : ታኅሣሥ 3 በዓታ ለማርያም
+++የአቡነ ዜና ማርቆስ እና የእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምበረከታቸው ምልጃ እና ፀሎታቸው ከሁላችን ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር +++
++በኀበ ኩሉ ዘተሰምየ መካነ ሰማዕተ መዋዕያን ወመካነ ጻድቃን ቡሩካን ወመካነ መላእክት ትጉሃን በኀበ ኩሉ መካን ርስት አንቲ ወሥሉጥ ስምኪ በኀበ እግዚአብሔር::++
+++++++++
++የድል ነሺዎች የሰማዕታት ቦታ በተባለ ሁሉ ዘንድ በቡሩካን ጻድቃን ቦታና በትጉሃን መላእክት ቦታ፡፡ በቦታው ሁሉ ዘንድ አንቺ ርስት ነሽ ፡፡ ስምሽም በእግዚአብሔር ዘንድ የሰለጠነ ነው፡++
...
የቅዱሳን አኗኗራቸው ድምጸ አራዊቱን ጸብዓ አጋንንቱን ግርማ ሌሊቱን ሳይሳቀቁ ደዋ ጥሰው፣ ደንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።” በዕብ.11፡37-38።
+++በረከትና ቃል ኪዳናቸው ምልጃቸው ከሁላችን ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር አሜን።++

በዓታ ለማርያም

                                    ዲያቆን መልአኩ እዘዘው
እመቤታችን በ5485 ዓ.ዓ ከአባቷ ከኢያቄም ከእናቷ ከሐና እም ሊባኖስ ትወጽዕ መርዓት፡፡ ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች” ተብሎ በተነገረው መሠረት ነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች፡፡ግንቦት አንድ ቀን ሊባኖስ በምትባል ወረዳ በብጽአት እንደተወለደች የቤተክርስቲያን ታሪክ በሰፊው ያስረዳል፡፡ በጾም በጸሎት በአስተብቁዖት የተገኘች ናት፡፡ ንጽሕት በመሆኗም ማኅደረ እግዚአብሔር ሆናለች፡፡
ከዚህ በኋላ እመቤታችን መዋዕለ ጥብ እስክታደርስ ድረስ በአባት እናቷ ቤት 3 ዓመት ተቀመጠች፡፡ ከመዝ ነበረት ውስተ ቤተ አቡሃ ወእማ 3ተ ዓመተ እንዘ ትጠቡ ሐሊበ እማ (እንዳለ በነገረ ማርያም፡፡)

ኢያቄምና ሐናም ልጃቸውን ሲያሰሳድጉና ስላደረገላቸውም ሁሉ እግዚአብሔርን ፈጽመው ሲያመሰግኑት ሦስት ዓመት ኖሩ። በጾም፤ በጸሎት ተወስነው ለድሆችና ለጦም አደሮች ምፅዋት እየሰጡ በጐ ሥራ መሥራትን አበዙ።

ልጃቸውንም ድንግል ማርያምን በንጽሕና ሲያሳድጉ ሦስት ዓመት በተፈጸመ ጊዜ ሐና ባሏን ኢያቄምንወንድሜ ሆይ ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር ብፅዐት አድርገን እንስጥ። ልጃችን ቤተ እግዚአብሔርን ልታገለግል እንጂ በዚህ ዓለም እኛን ልታገለግል እንዳልተሳልን አስብ አለችው።ኢያቄምም ይህን ነገር ከሚስቱ በሰማ ጊዜ ደስ አለው።


ነብየ እግዚአብሔር ዳዊት ልጄ ሆይ ስሚ እዪ ጆሮሸንም አዘንብዪ ወገንሽን የአባትሽንም ቤት እርሺ ንጉሥ/ክርስቶስ/ ውበትሽን /ንጽሐ ባሕርይሽን/ ወድዶአልና መዝ 44÷10-11 ብሎ እንደተናገረ ለወላጆቿ የብፅዐት ልጅ የሆነችው ድንግል ማርያም ሆዷ ዘመድ ሳይወድ አፏ እህል ሳይለምድ ከእናቷና ከአባቷ ተለይታ ታህሣሥ ሦስት ቀን በሦስት ዓመት ወደ መቅደሰ ኦሪት ገብታለች። በአታ ለማርያም ማለትም የድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ መግባት ማለት ነው።

ከዚህም በኋላ በ3 ዓመት ልተተ ሕፃናትን ፈጸመች አበ እመ እያለች ታጫውት ጀመር እነርሱም ከእንግዲህ ወዲህማ ስእለት መብለት ይሆንብን የለምን ወስደን እንስጥ ብለው ይዘዋት ወደ ቤተ መቅደስ ሲሄዱ ዘካርያስም ሕዝቡን ሰብስቦ ጉባዔ አድርጎ ሲያስተምር ቆያቸው ከዚያውም ደርሰው እነሆ ተቀበሉን አሏቸው እነርሱም እንቀበላለን ብለው ቢያዩዋት ከፀሐይ 7 እጅ አብርታ ዕንቈ ባሕርይ መስላ ታያቻቸው እነርሱም እኛ ይህችን የመሰለች ፍጡር ምን እናደርጋታለን ምን እናበላታለን ምን እንጋርድላታለን ብለው ሲጨነቁ ከዚህም መካከል እመቤታችንን እግዝእትነ ማርያም መንፈሳዊ ረኅብ ተነስቶባት ምርር ብላ አለቀሰች፡፡

ያን ጊዜ መልአኩ ፋኑኤል በመሶበ ወርቅ ኅብስት ሰማያዊ ፤ በብርሃን ጽዋ ስቴ ሕይወት ይዞ ረቦ ታያቸው ሕዝቡም ዘካርያስን አባታችን ይህ የወረደው ክብር ላንተ እንደሆነ ተነስተህ ታጥቀህ እጅ ነስተህ ሰግደህ ተቀበል አሉት፡፡ ዘካርያስም እሽ ብሎ እጅ ነስቶ ሰግዶ እቀበላለሁ ብሎ ሲያይ ወደሰማይ እራቀው መጠቀው፡፡ ከሕዝቡም እያንዳንዱ እየተነሱ እንቀበላለን ብለው ቢያዩ ወደሰማይ ራቃቸው መጠቃቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ዘካርያስ ሐናን ጠርቶ ለናንተ ለእንግዶች የወረደ ክብር እንደሆነ ሕፃኒቱን ይዘሽ ወደዚያ ፈቅ ብለሽ ተቀመጪ አላት፡፡ እርሷም ሕፃኒቱን ይዛ ወደዚያ ፈቅ ብላ ተቀመጠች፡፡ መልአኩም ከራሳቸው ላይ ረቦ አልወርድም አለ፡፡

Monday 10 December 2012

ኤልያስ

ኤልያስ
እነሆ የተባረከ የታህሳስ ወር ባተ፤ ይህ ወር ቀኑ 9 ሰዓት ነው ሌሊቱ 15 ሰዓት፤ ቀኑ በጣም አጭር ነው ፤ ቶሎ ይመሻል ሌሊቱ በጣም ረጅም ነው፤ ታህሳስ 1 በዚህች ቀን በገለዓድ ይኖር የነበረው ቴስብያዊው ኤልያስ የተወለደበት ቀን ነው፤ ታሪኩ 1ኛ ነገስት 17፤1 ላይ በስፋት ይገኛል፤ በእሳት ሰረገላ የተሰወረው ጥር 6 ቀን ነው፤ እነዚህን ሁለት ቀናት ቤተክርስቲያን ነብዩን አስባ ትውላለች፤ ይህ ነብይ በአገራችን በስሙ የታነጹለት አብያተክርስቲያናት አሉት:: ከነዚህም በመዲናችን አዲስ አበባ እንጦጦ ጋራ ላይ የሚገኘው ቤተክርስቲያን አንዱ ነው፤ ኤርትራ ውስጥም አንድ ቤተክርስቲያን አለው፤ ዛሬ በደማቁ ተከብሮ ይውላል፡፡ አክአብና ኤልዛቤል ምሰኪኑን ናቡቴ ከአባቶቹ እርስት አፈናቅለው በግፍ በገደሉት ጊዜ፤ ንጉሱን ሳይፈራና ሳያፍር በግልጽ የዘለፈ ነብይ ነው፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይንም የለጎመ ነው ይህንንም ያዕቆብ በመልእክቱ እንዲህ ሲል መስክሯል ያዕ 5 ፤ 16 "የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች። ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች"

ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን፡፡

Saturday 8 December 2012

ተፍጻሚ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ

ተፍጻሚ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ህዳር 29 አረፈ::
ተፍጻሜ ሰማዕት ጴጥሮስ ሦስት ደቀ መዛሙርት ነበሩት አርዮስ፤አኪላስና እለእስክንድሮስ ይባላሉ::
ለአርዮስ ክህነት ሰጥቶ የሾመው ተፍጻሜ ሰማዕት ጴጥሮስ ነው:: አርዮስ ግን አጥብቆ ተመራመረ ወልድ ፍጡር ነው ብሎ ወደቀ::
አርዮስ ወልድ ፍጡር ነው ብሎ በድብቅ ለሰው ማስተማር ጀመረ:: በዚህ ጊዜ ጌታችን ለተፍጻሚተ ሰማዕት ጴጥሮስ የተቀደደ ልብስ ለብሶ ተገለጸለት
ተፍጻሚ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ :- አንተ ማን ነህ?
...
ኢየሱስ :- የናዝሪቱ ኢየሱስ ነኝ
ተፍጻሚ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ :- ታዲያ ልብስህ ለምን ተቀደደ ?
ኢየሱስ :- “አርዮስ ሰጠጣ ለልብስየ” አርዮስ ልብሴን ቀደደው :: ከባህሪ አባቴ ከአብ ከባህሪ ህይወቴ ከመንፈስ ቅዱስ ለይቶ ፍጡር ነው አለኝ ::
ተፍጻሚ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን ራዕይ እይቶ ብዙም ሳይቆይ አርዮስ መጣ ቁጭ አድርጎ መከረው “በልብህ ያለውን ኑፋቄ ካሰብክ እንዳትናገር ከተናገርክ እንዳትደግመው ብሎም ያስጠነቅቀዋል፤ ሊሰማው ግን አልቻለም፤ አውግዞ ይለየዋል:

Tuesday 4 December 2012

ቅዱስ መርቆሪዎስ ሰማዕት

+ህዳር 25 ቀን ቅዱስ መርቆሪዎስ በሰማዕትነት አረፈ፤ አገሩ ሮም ነው፤ በወጣትነቱ ከሃዲው ንጉስ ኡልያኖስ ላቆመው ጣኦት አልሰግድም ብሎ የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለውን መከራ ተቀበለ፤በመጨረሻም ህዳር 25 ቀን አንገቱን ቆርጠው ገደሉት ደም ውኃና ወተት ከአንገቱ ፈሰሰ። ይህ ሰማዕት በአገራችን በስሙ በርካታ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት አሉት በተለይም ቅዱስ ላሊበላ ካነጻቸው 11 ውቅር አብያተክርስቲያናት አንዱን ቤተ መርቆሪዎስ ብሎ ሰይሞለታል፤ በዚህ በሰሜን ሸዋ ደግሞ የሚገርም ገዳም አለው፤ ካህናት በማህሌት ወረብ ሲያቀርቡ ስዕሉ ያሸበሽባል ይዘላል፤ ይህንንም አይቶ ማረጋገጥ ይቻላል፤ በመዲናችን አዲስ አበባ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ታቦቱ አለ:: ዛሬ በደማቁ ተከብሮ ይውላል። መርቆሪዎስ ከሞተ በኃላ ፈረሱ ለሰባት ዓመት ወንጌልን አስተምሯል፤ በኃላም አንገቱን ቆርጠው ገድለውታል እንዴት ብሎ የሚገረም የበልአምን አህያ ይጠይቃት፤ እኛስ እስመ አልቦ ነገር ዘይሳኣኖ ለእግዚያብሔር ብለን እንመልሳለን፤ ዘኁልቁ 22፤28 ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አለ ቃል የሌለው አህያ በሰው ቃል ተናግሮ የነብዩን እብድነት አገደ ይላል 2ጴጥ 2፤16። ከ ከሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሪዎስ  አመታዊ በዓል  በረከት ያሳትፈን አሜን !!!