ጥቅስ

ጌታዬ
እግዚአብሔር ሆይ
እስከዚህ ያደረስኸኝ
እኔ ማን ነኝ ?
ቤቴስ ምንድር ነው?
2 ሳሙ 7፥18

Wednesday 12 December 2012

ታኅሣሥ 3 እረፍቱ ለአቡነ ዜና ማርቆስ

ታኅሣሥ 3 እረፍቱ ለአቡነ ዜና ማርቆስ : ታኅሣሥ 3 በዓታ ለማርያም
+++የአቡነ ዜና ማርቆስ እና የእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምበረከታቸው ምልጃ እና ፀሎታቸው ከሁላችን ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር +++
++በኀበ ኩሉ ዘተሰምየ መካነ ሰማዕተ መዋዕያን ወመካነ ጻድቃን ቡሩካን ወመካነ መላእክት ትጉሃን በኀበ ኩሉ መካን ርስት አንቲ ወሥሉጥ ስምኪ በኀበ እግዚአብሔር::++
+++++++++
++የድል ነሺዎች የሰማዕታት ቦታ በተባለ ሁሉ ዘንድ በቡሩካን ጻድቃን ቦታና በትጉሃን መላእክት ቦታ፡፡ በቦታው ሁሉ ዘንድ አንቺ ርስት ነሽ ፡፡ ስምሽም በእግዚአብሔር ዘንድ የሰለጠነ ነው፡++
...
የቅዱሳን አኗኗራቸው ድምጸ አራዊቱን ጸብዓ አጋንንቱን ግርማ ሌሊቱን ሳይሳቀቁ ደዋ ጥሰው፣ ደንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።” በዕብ.11፡37-38።
+++በረከትና ቃል ኪዳናቸው ምልጃቸው ከሁላችን ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር አሜን።++

No comments:

Post a Comment